×

Warning

JUser: :_load: Unable to load user with ID: 42
Sunday, 13 November 2011 21:20

የአቶ መርኪና መጃ ግለ ታሪክ - ክፍል አንድ Featured

Rate this item
(0 votes)

የመጽሐፍ ግምገማ

የአቶ መርኪና መጃ ግለ ታሪክ - ክፍል አንድ

 

አቶ መርኪና በሰማንያ ሦስት ዓመታቸው በኅዳር ወር 2000 ዓ.ም. ወደ ጌታ ተሻግረዋል። በቀብራቸው ሥርዓት ላይ ከስምንት ሺህ በላይ ሰው እንደ ተገኘ ታውቋል። ይህ ክፍል “የአቶ መርኪና መጃ ግለ ታሪክና የወላይታ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን ታሪክ” በሚል ግለሰቡ ጽፈው በ 2000 ዓ.ም. ከታተመው መጽሐፍ የተቀነጨበ ነው። ከዚህ ቀደም እንዳደረግነው ሁሉ መጽሐፉን ከመገምገም ይልቅ ከተለያዩ የመጽሐፉ ክፍሎች ቆንጽሎ በማስነበብ አንባቢዎቻችንን በጌታ ሥራ ማደፋፈር የተሻለ እንደ ሆነ ተገንዝበናል። ከ 13 ዓመት በፊት አቶ አማኑኤል አብርሃም “የሕይወቴ ትዝታዎች” በሚል ርዕስ በእንግሊዝኛ ካሳተሙት መጽሐፍ ጋር ተመሳሳይነት አለው። የሚያስገርመው ሁለቱም መሪዎች በቅርብ መተዋወቃቸው ነው፤ ለምሳሌ፣ መርኪና በ ገጽ 44 ላይ ስለ አማኑኤል ያሉትን እንመልከት፦

 

“አንድ ቀን የሚስዮኑ ኃላፊዎች፣ “በታንዛንያ ለሚካሄደው የሉተራን ቤተ ክርስቲያን ታላቅ ስብሰባ የሲዳማን ቤተ ክርስቲያን ወክለህ እንድትገኝ ተጠርተሃል፣ ጉባኤው የሚካሄደው በክሊማንጃሮ ተራራ አጠገብ ነው” አሉኝ። እኔም ተደነቅሁና፣ “ከእነዚያ ታላላቅ ሰዎች ጋር ጉባኤውን ለመካፈል እኔ ምን ዕውቀትና ችሎታ አለኝ? የእግዚአብሔር ፈቃድ ከሆነ፣ ወደሚልከኝ ቦታ ሁሉ እሄዳለሁ” ብዬ “እሺ” አልኩኝ። ተነሥቼ የሚስዮኑ መሪዎች ጉባኤው ወደሚካሄድበት አገር ለመጓዝ ወደሚዘጋጅበት ወደ አዲስ አበባ ሄድኩኝ። ዶ/ር አማኑኤል አብርሃም እና ዶ/ር አማኑኤል ገ/ሥላሴ ከሚሄዱት መካከል ነበሩ። ለጉዞው ከመነሣታችን በፊት ዶ/ር አማኑኤል አብርሃም በመኖሪያ ቤታቸው የእራት ግብዣ አደረጉልን። በሕይወቴ እንደዚያ ዓይነት ግብዣ አይቼ አላውቅም። እሳቸው በጊዜው በኢትዮጵያ መንግሥት የተሾሙ ሚኒስትር ነበሩ። በድሆች መካከል ክርስቶስ ራሱን ዝቅ እንዳደረገ፣ እርሳቸው በእኛ መካከል ራሳቸውን ዝቅ ያደረጉ ነበሩ።”

 

ሁለቱም መጽሐፎች በድምሩ ቢያንስ የመቶ ዓመት የቤተክርስቲያንን ታሪክ ከነበረው ማሕበራዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ጋር በማያያዝ ይተረጉማሉ። ሁለቱም ጸሐፊዎች በሂደቶቹ ውስጥ ታዛቢ ብቻ ሳይሆኑ መሪዎችም ስለ ነበሩ ያቀረቡልንን ሠነድ ጠቃሚነት አጉልቶታል። በኛ አስተያየት ይህን መሰል መጽሐፎችን በቤተክርስቲያን አመራር ላይ የሚገኙ ሁሉ በጥንቃቄ ሊያነብቡ ይገባል። በመጽሐፍ ቅዱስ ትምሀርት ቤቶችና ሴሚናሪዎች እንደዚሁም የመሪነት ሥልጠና በሚሰጡባቸው ቦታዎች ሁሉ ዋነኛ የመማርያና የመወያያ መጽሐፎች ሆነው ሊቀርቡ ይገባል። የሁለቱን መሪዎች አመራር በጥንቃቄ መመርመር ተገቢም ጠቃሚም ነው። እነዚህን ዓይነት አገልጋዮች ስለ ሰጠን አምላካችንን በብዙ ልናመሰግነው ያስፈልጋል። በተጨማሪም አልተተረጎሙ እንደ ሆነ የአቶ አማኑኤል ወደ አማርኛ፣ የአቶ መርኪና ደግሞ ወደ እንግሊዝኛ ሊተረጎሙ ይገባል እንላለን። ጽሑፉን እንድናዳርስ ላስቻሉን ሁሉ ምስጋናችን ይድረሳቸው። የመርኪ ታሪክ እነሆ፦

 

አቶ መርኪና መጃ ተወልደው ያደጉት በደቡባዊ ኢትዮጵያ በወላይታ ዞን ነው። የአቶ መርኪና አባት አቶ መጃ ማዴሮ በ 1888 ዓ.ም. ከአቶ ማዴሮ ሃናቆ እና ከወ/ሮ አሽሬ ዳኖሌ ተወለዱ። አቶ መጃ ነገሮችን ፈጥነው የመረዳት ችሎታ የነበራቸው አስተዋይ ሰው ስለ ነበሩ፣ ሰዎች ከቅርብና ከሩቅ እየመጡ የምክር አገልግሎትን ከእርሳቸው ያገኙ ነበር። መልካም ባሕርያቸውም በኅብረተሰቡ መካከል አክብሮትን እንዲያገኙ አድርጎአቸዋል።

 

አንድ ቀን አባቴ ክርስቲያን ከመሆኑ በፊት ብዙ ክፉ ሥራዎችን ይሠራ እንደ ነበር ነገረኝ፤ እኔም ክፉ ሥራ ሠርቼ እንደ ነበር ተገነዘብኩ። ወንጌል ወደ ማኅበረሰባችን ከመድረሱ በፊት በጨለማ ሕይወት ውስጥ እንኖር ስለ ነበረ፣ የተሻለው ነገር ምን እንደ ሆነ አናውቅም ነበረ። ከዚህም የተነሣ ሕይወታችን ጎስቋላና በፍርሃት የተሞላ ነበር። ከበሽታና ከሞት ለማምለጥ፣ አዝመራችን የበለጠ ምርት እንዲሰጠንና ሌላም ብዙ የሕይወት ውጣ ውረዶችን ለማለፍ መልካም መናፍስትንና ክፉ መናፍስትን መለማመን ነበረብን። ታላቅ እንደ መሆኔ መጠን፣ መሥዋዕት ለማቅረብ ከአባቴ ጋር የምሄደው እኔ ነበርኩ። በእኛ አካባቢ የታወቁ ሰዎች ወደ ፈለጉት አቅጣጫ አንድን ሰው አስከትለውና በቅሎ ላይ ተቀምጠው ይሄዱ ነበር። የአባቴን ካባ ተሸክሜ ከበቅሎአቸው ኋላ የምከተለው እኔ ነበርኩ። በእናቴ ቤተሰቦች በኩል አንድ ስሕተት ቢፈጸም ለመሥዋዕት የሚሆን በግ ይቀርባል። በአባቴ ቤተሰቦች በኩል ደግሞ ክፉ ሥራ ቢሠራ ወይፈን ይታረዳል። ከታረደው እንስሳ የተለያዩ ብልቶች ተወስደው ይጠበሱና ጠንቋዩ ይቀመጥ ባለበት ስፍራ ይቀመጣል። መስዋዕቱ ለሰይጣን የሚቀርብ ከሆነ ፍየል ይታረድና ሥጋው ጠንቋዩ ባዘዘበት ቦታ ይደረጋል። የበቆሎ እሸት እንደ ደረሰ ለዓመቱ ምስጋና የማቅረብ ሥርዓት ይካሄዳል። በቆሎውን ከነገለባው ጠብሶ ወይም ቀቅሎ በመንገድ ዳር ወይም ቤተሰብ ተሰብስቦ በሚያመልክበት ዛፍ ሥር ያኖሩታል። በተጨማሪም አባቴ ጣቶቹን በማር ውስጥ በማጥለቅና ወደ ሰማይ በመርጨት የጣዖት አምላክን ይለምን ነበር። የተረጨው ማር ተመልሶ ሲወድቅ ሮጬ ሄጄ ለመብላት እከጅላለሁ። ሆኖም አባቴ ያየኝ ይሆናል ብዬ እፈራ ስለ ነበር እተወዋለሁ።

 

በ1927 ዓ.ም. አንድ ቀን አባቴና እኔ ወደ ቤታችን ስንሄድ አረፋማውን ጅረት እየተከተልን ወደ ምንጩ አመራንና የአቶ አጌዶን ቤት ስናልፍ አቶ ዋንዳሮ ዳባሮ በአቶ አጌዶን ቤት ውስጥ ወንጌልን እየሰበኩ ኖሮ እኔና አባቴን አይተው ገብተን እንድንሰማ ጋበዙን። እኛም ተስማማን፣ ነገር ግን አባቴ እኔን በቅሎውን እንዳስር ሲያዝዘኝ ልጓሙን ፈትቼ እግሩን በገመድ በዛፍ ግንድ ላይ አሰርኩና ገብተን ለመስማት ተቀመጥን። አቶ ዋንዳሮ ስብከታቸውን ቀጠሉና በመካከሉም መዝሙር ጣልቃ እያስገቡ ያዘምሩ ነበር። ከመዝሙሮቹ አንዱ እንዲህ የሚል ነበር፦

     

በጎቹ የኢየሱስ ክርስቶስን ድምጽ ሲሰሙ

      ሊከተሉት ተፋጠኑ

      አስቀድመው ድምጹን ያልሰሙ ሊደርሱባቸው ተቻኮሉ

      እግዚአብሔርም ጠራቸውና ራሱን ገልጦላቸው ምሥጋናቸውን በደስታ ተቀበለ።

 

ሰባኪው ለረዥም ጊዜ ቢናገሩም እኔ የማስታውሰው ዋና ነጥብ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ወደዚች ዓለም አንድ ቀን ይመጣል የሚለውን ነበር። የሚያምኑትንም ከእርሱ ጋር ወደ ሰማይ ይወስዳቸዋል። በእርሱ የማያምኑትን ደግሞ በእሳት ባሕር ውስጥ ይጥላቸዋል። “እናንተ ሰይጣንን ማምለክ አቁማችሁ በጌታ ኢየሱስ እመኑ። አለበለዚያ ግን ከሰይጣን ጋር ወደ እሳት ትጣላላችሁ። ዛሬውኑ ማመን አለባችሁና ፍጠኑ፤” እያሉ ያስጠነቅቁ ነበር።

 

በማጠቃለያውም፣ ስንቶቻችን በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ለማመን እንፈልግ እንደ ሆነ ጠየቁን። ብዙ ሰዎች እጆቻቸውን አወጡ፤ አባቴና እኔም እጆቻችንን አነሣን። አቶ ዋንዳሮም ስብከታቸውን ቀጠሉ። አሁን ሁላችሁም በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በእርግጥ እናምናለን የምትሉ ከሆነ፣ ሰይጣንንና መላእክቱን ማምለክ አቁሙ። እባካችሁ እኔ የምለውን ቃል ከእኔ በኋላ ድገሙ።

 

“አሁን ሰይጣንን ክጃለሁ። በኢየሱስ ክርስቶስም አምናለሁ። እርሱ ለኃጢአቴ እንደ ሞተልኝ አውቃለሁ። ከኃጢአቴም እንዲያነጻኝ እፈልጋለሁ፤ ዳግመኛ ሰይጣንን አላመልክም፤ ነገር ግን ኢየሱስን እከተለዋለሁ፤ እታዘዘዋለሁም” እያልን ደገምን። ከዚያም ከኢየሱስ ጋር ለመኖር እንዲረዳን አንዳንድ ቀላል መመሪያዎችን ሰጡን። ወደ ቤታችሁ ሂዱና በቤታችሁ ውስጥ የሚገኙትን ለጣዖት አምልኮ የምትጠቀሙባቸውን ቁሳቁሶች አውጥታችሁ ጣሉ። ሁሉንም አቃጥሉት፤ ከዚያም ምግባችሁን በምትመገቡበት ጊዜ፣ ሥራችሁን በምትጀምሩበት ጊዜ፣ እንዲሁም ማንኛውንም ነገር ለመሥራት በምታቅዱበት ጊዜ፣ እግዚአብሔር እንዲመራችሁና እንዲባርካችሁ በጸሎት ጠይቁት። በጸሎታችሁም መደምደሚያ ላይ ይህንን ሁሉ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እንጠይቅሃለን ካላችሁ በኋላ “አሜን” ብላችሁ ደምድሙ። በተጨማሪም በጉልበታችሁ ተንበርክካችሁ ማጎንበስ ጥሩ ነው። ስትጸልዩም ዓይኖቻችሁን ትጨፍናላችሁ፣ ካሉን በኋላ ቡና አቀረቡልንና ከመጠጣታችን በፊት ለእኛ እንዳስተማሩን ሲጸልዩ ሰማናቸው። ወደ ቤታችን እንደ ገባን፣ የሆነውን ሁሉ ለመላው ቤተሰብ አስረዳንና እነርሱም በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ እንዲያምኑ አጥብቀን ገፋፋናቸው። ታላቅ ደስታም ተሰማን። በቤታችንም ውስጥ ሁሉ ነገር አዲስ መሰለ። እናቴ ቡና አፍልታ “እንጸልይ” አለችን።

 

አባቴም ደግሞ ተንበርክኮ ጸለየና ሁለታችንም ድምጻችንን ከፍ አድርገን፣ “አሜን” አልን። ቤተሰቡ በሙሉ ተደነቁና ምን እንደምናደርግና ወደ ማን እንደምንናገር ጠየቁን። እኛም የተቻለንን ያህል ልናስረዳቸው ሞከርን። እኛ የምንናገረውና የምንጸልየው ጌታ ኢየሱስ ወደሚባለውና የእግዚአብሔር ልጅ ወደ ሆነው፣ እንዲሁም ከሰማይ ወደ መጣው ነው። እርሱ ለኃጢአታችን ሲል ሞቷል፣ ከሞትም ተነሥቷል፤ ወደ ሰማይም ሄዷል፤ ነገር ግን ተመልሶ ይመጣል። የሚያምኑትንም ከእርሱ ጋር ወደ ሰማይ ይወስዳቸዋል። የማያምኑትን ደግሞ በእሳት ባሕር ውስጥ ያቃጥላቸዋል። እናንተም ደግሞ በእርሱ እመኑና ዳኑ ብለን ተናገርን። ወዲያውም አባቴ ተነሣና ሰይጣንን ያመልክ በነበረ ጊዜ ይጠቀምባቸው የነበሩትን ጥቃቅን ዕቃዎችና የተሰቀለውን ልብስ ጨምሮ ወሰደ። እነዚያ ዕቃዎች ሁሉም ወንበዴውን ገድሎ የወሰዳቸው ናቸው። ሁሉንም ሰብስቦ ዥው ባለ ገደል ውስጥ ከተታቸው። ዕቃዎቹ ስለ አሮጌው ሕይወቱ የሚያወሱ ነበሩና ሁሉንም አስወገዳቸው።

 

እናቴና በቤት ያሉት ልጆች በሙሉ ልባቸው በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ለማመን ከአንድ ወር በላይ አልወሰደባቸውም። እናቴንና የቀሩትን ልጆች በሙሉ በተለይ ያሳመናቸው ነገር ቢኖር በአባቴ ላይ ያዩት ትልቅ ለውጥ ነበር። አባቴ አስቀድሞ የነበረው ባሕርይ፣ አንድ ነገር ሲበላሽ በእናቴ ላይ ይጮህና ይቆጣ ነበር። ልጆቹ በሙሉ ይፈሩት ነበር። አሁን ግን ፍጹም ተለወጠና በጣም ደግ ሰው ሆነ። በእኔም የሚታየው ለውጥ ግልጽ ነበር። ለእናቴ ልጆች በሙሉ ጥሩ አልነበርኩም። ከቤት ውስጥም አንዳንድ ነገሮችን እሰርቅ ነበር፤ አሁን ግን በእውነት ተለወጥኩ። “እናንተ ቀድሞ ወገን አልነበራችሁም፤ አሁን ግን የእግዚአብሔር ወገን ናችሁ፤ እናንተ ምሕረት ያገኛችሁ አልነበራችሁም፤ አሁን ግን ምሕረትን አግኝታችኋል” ይላል። [1ኛ ጴጥሮስ 2፡10]

 

ማሳሰቢያ፦ በዚህ ክፍል የሚከተሉትን ነጥቦች በጥሞና እናስተውል፦ የመዝሙርና የቃሉን ጥምረት። የአባትና የልጅ ፍቅር። ለእግዚአብሔር ቃል ያለውን ጥማትና አክብሮት። ለመማር ያለውን ፍላጎትና ምክንያት። ቃሉን ለማስተማር ያለውን ትሕትናና ቅንነት። የገቡትን ቃል ስለ መጠበቅ። ከግል ጥቅም ጋር ሳይያያዝ እግዚአብሔርና ሰውን ስለ ማገልገል።

 

ክርስቲያኖች ይዘምሩ የነበሩትን መዝሙሮች መዘመር ወደድን። አንድ ጊዜ ወደ አቶ ጉንታ ቤት ሄድንና አዲስ መዝሙር ተማርን። ወደ ቤታችን ስንመለስ በመንገዳችን ሁሉ እየዘመርን ስንሄድ፣ የመዝሙሩን ዋና ቃል እንደ ረሳን አስተዋልን። መዝሙሩን በሚገባ ለማወቅ ከነበረን ፍላጎት የተነሣ ተመልሰን ወደ አቶ ጉንታ ቤት ረዥም ጉዞ አደረግን። ወደ ቤቱ በደረስን ጊዜ ግን አቶ ጉንታ በከባድ እንቅልፍ ላይ ነበር። የመዝሙሩ ቃላት ተረስቶናልና እባክሽን ቀስቅሽልንና አንደ ጊዜ ዘምሮልን ቃሉን እንያዝ፣ እርሱም ተመልሶ ይተኛል ብለን ባለቤቱን ለመንናት። እርሷም ከእንቅልፉ ቀሰቀሰችልንና ተነሥቶ መዝሙሩን አዜመልን። ከዚያም አባቴ፣ ወንድሜና እኔ ወደ ቤታችን ተቻኮልን፤ በመንገዳችንም እየዘመርን ሄድን፤ ወደ ቤታችን በደረስንም ጊዜ መዝሙሩን በሚገባ መዘመር ችለን ነበር።

 

      ጌታችን ከሰማይ ወረደ

ከድንግል ማርያም ተወለደ

በመስቀል ላይ ሞተ፣ ሞትንም አሸነፈ

ኃጢአታችንን ተሸከመልን

ተነሣና ወደ ሰማይ ዐርጓል

ተመልሶ ይመጣል

ቅዱሳኑን ለመውሰድም አይዘገይም

 

አዲስ ባገኘነው እምነታችን ለማደግ ከእግዚአብሔር ቃል የበለጠ መማር እጅግ አስፈላጊያችን ነበር። ጎረቤታችን አቶ ጉንታም በታማኝነት አስተምረውናል። እኛም ውስብስብ የሆነውን የአማርኛ ፊደል መማር ጀመርን፤ ምክንያቱም መጽሐፍ ቅዱስ የተጻፈው በእነዚህ ፊደላት ስለ ነበር ነው። አባቴ ወደ እራሾ ቤት ሄጄ ፊደልን እንድማር ነገሮችን አመቻቸልኝ። አቶ እራሾ አስቀድሞ ማንበብ የቻለ ስለ ነበር፣ ለጌታ ካለው ፍቅር የተነሣ በፍቃደኝነት የምሥጋና መዝሙሮች ይዘምራል፣ ወንጌልን ይሰብካል፤ እንዲሁም ያለ ክፍያ የአማርኛ ፊደልን ያስተምራል። ለብዙ ቀናት ወደዚያ ስሄድ የምደርሰው ሌሎች ልጆች ተምረው ወደየቤታቸው ተበታትነው ነበር፤ ምክንያቱም ወደ ፊደል መማሪያ ቦታ ከመድረሴ በፊት የምሠራቸው ብዙ አሰልቺ ሥራዎች ስለነበሩብኝ ነው። ብዙ ሳንቆይ ማንበብ ቻልንና የእግዚአብሔርን ቃል የበለጠ እየተረዳን ሄድን። አባቴም በስተ እርጅናው ማንበብ እንደ ሌሎቹ ተማረ። እግዚአብሔርም ምን እንዳደረገልን፣ እርሱን ከሚከተሉትም ጌታ ምን እንደሚፈልግ ማወቅን በጣም እንራብ ነበር።

 

ከጥቂት ጊዜያት በኋላ አባቴና እናቴ ተጠመቁ። እኔም አብሬአቸው ለመጠመቅ ብፈልግም፣ እነርሱ ግን አንተ ገና ልጅ ነህ ብለው አገዱኝ። በደንብ ማንበብ ስትችል ያኔ ትጠመቃለህ አሉኝ። እኔም በጣም ተረብሼ እያለቀስኩ እጠመቅ ዘንድ ለመንኳቸው። ለማግባባት ግን አለመቻሌን በተረዳሁ ጊዜ፣ “ጌታ ሆይ፣ ቶሎ ለማንበብ እንድችል እርዳኝ። ለመጠመቅ እንድችል ብትረዳኝ በቀሪው የሕይወት ዘመኔ አገለግልሃለሁ” ብዬ ጸለይኩ።

 

ከአቶ እራሾ ጋር መማሬን ቀጠልኩኝ። ከእርሱም ጋር ከቦታ ወደ ቦታ መዘዋወር ጀመርኩኝ። በመጀመሪያ አብሬው እየሄድኩኝ እርሱ በሚሰብክበት ጊዜ እኔ በቅሎውን እጠብቅለት ነበር። ከጥቂት ጊዜ በኋላ ግን በቅሎውን ሌሎች ክርስቲያኖች እየጠበቁ፣ እኔ ፊደል በማስቆጠር እረዳ ነበር። በኋላም ቁንጠሌ በአቶ ፍንጦ ቤት ቆይቼ እዚያ በምትገኘው ቤተ ክርስቲያን እሰብክና አስተምር ነበር። በጨራቂ አካባቢ ከአቶ እራሾ ጋር ስዘዋወር ብዙ ጊዜ በተለያዩ ስፍራዎች ወንጌልን ሰብኬአለሁ። ማንበብና መጻፍ እንደ ቻልኩ፣ ከመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ብዙ ክፍሎችን ለማንበብ በቃሁ። ከዚያም እንድጠመቅ ተፈቀደልኝ። ይህ የሆነው በ1932 ዓ.ም. ሲሆን፣ ጋቼኖ በሚባለው ቦታ ሎላሞ ቦቄ እና ፉላሶ የሚባሉ፣ ከሁምቦ ቤተ ክርስቲያን መጥተው አጥምቀውኛል። ከተጠመቅሁ በኋላ ወደ ዋንቼ ፈጥኜ በመሄድ ደስታዬን ለወላጆቼ አካፈልኳቸው፤ እነርሱም ተደሰቱ። መታወቅ ያለበት በዘመኑ የተቀናጀ እውቀት (ትምህርት) ባልነበረበት በዚያ በኢትዮጵያ ክፍል ቤተ ክርስቲያን ራሷ ማንበብና መጻፍ ታስተምር ነበር። በዚህም ብዙ ወጣቶች ማንበብና መጻፍ ከመቻላቸውም በላይ፣ የአማርኛን ቋንቋ ለማወቅ ችለዋል። በእነዚያ ቀናት ቤተ ክርስቲያን ማደግ ጀመረች፤ ብዙ ወጣቶችና ጎልማሶችም ማንበብ ችለዋል። በአንድ እሑድ ከዋንቼ ቤተ ክርስቲያን 70 ሰዎች ተመርጠው ጥንድ ጥንድ እየሆኑ በ 4 አቅጣጫዎች ተላኩ። ለሚያገኙት ሁሉ በመንገድ ላይም ይሁን በቤት ውስጥ ወንጌልን መስበክ ነበረባቸው። ሲመለሱም ለእኛ ቤተ ክርስቲያን ዘገባቸውን ማቅረብ ነበረባቸው። አቶ ቶማ ቡሬ እና እኔ ወደ ሁምቦ ሄድን። የሐማሳን ወንዝ እንደ ተሻገርን፣ ሰዎች ተሰብስበው አገኘን። አግባብተናቸው፦ “ከእግዚአብሔር ቃል ልናስተምራችሁ ነው የመጣነው፣ ለመስማት ትፈልጋላችሁን?” አልናቸው።

 

ሰዎቹም ለመስማት ጓጉተው ነበርና እንድናስተምራቸው ጋበዙን። አቶ ቶማ ጸልዮ ከዘመረላቸው በኋላ እኔ ተነሣሁና ክርስቶስ ሰዎችን ከኃጢአታቸው ለማዳን እንዴት እንደ መጣ ከእግዚአብሔር ቃል አስተማርኳቸው። ትምህርቱን እንደ ጨረስኩ፣ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን እንደ ግል አዳኝ አድርጎ ለመቀበል የሚሻ ከመካከላቸው እንዳለ ጠየቅሁኝ። ጥቂት ሰዎች እጆቻቸውን አነሡ፤ እኔም ሰይጣንን ክደው ኢየሱስ ክርስቶስን እንደ ግል አዳኛቸው አድርገው ለመቀበል የሚሹ ከመካከላቸው እንዳሉ ዳግመኛ ጠየቅሁኝ። ጥቂት ሰዎች እጆቻቸውን አነሡና ሰይጣንን ክደው ኢየሱስ ክርስቶስን እንደ ግል አዳኛቸው አድርገው እንዲቀበሉ በጸሎት መራናቸው። በቤታቸውም ውስጥ ለሰይጣን አምልኮ ያስቀመጡአቸውን ዕቃዎች እንዲያስወግዱ አስተማርናቸውና ከቤታቸው አውጥተው እንደሚጥሉም ቃል ገቡ። በየሳምንቱ እሑድ እየሄድን እንደምናስተምራቸው ነግረናቸው ጉዞአችንን ወደ ሌላ ቦታ አደረግን። የዚያን እሑድ ጉዞአችን ከተለያዩ ብዙ ቡድኖች ጋር እንድንገናኝ አድርጎናል። ማንቴ ኮቴ በሚባለው ቦታ ብዛት ያላቸው ሰዎች በአንድ ቦታ ተሰብስበው አገኘንና ከእግዚአብሔር ቃል ልናስተምራቸው እንደምንፈልግ ገልጸን ፈቃደኝነታቸውን ጠየቅናቸው። እነርሱም ፈቃደኝነታቸውን ገለጹልን። መዝሙር ከዘመርን በኋላ ስለ ደኅንነት ማስተማር ጀመርን። እግዚአብሔር ልጁን ስለ ኃጢአታቸው አሳልፎ እንደ ሰጠ፣ ነገር ግን ሁላችንም ኃጢአተኞች ነንና አዳኝ ያስፈልገናል ብለን የተቻለንን ያህል በግልጽ ካስተማርናቸው በኋላ፣ በየሳምንቱ እየመጣን እንደምንከታተላቸው ቃል ገባንላቸው። ከዚያም ከሌላ አካባቢ የተከናወነውን ሥራ ለመስማት ወደ ቤት አመራን። በዋንቼ ቤተ ክርስቲያን የቀሩት አማኞች ቀኑን ሙሉ እየጸለዩልን ነበር። ከሰዓት በኋላ ክርስቲያኖቹ ወንጌልን ለመስበክ ለሄዱት 70 ሰዎች ምግብና ቡና በማዘጋጀት ሥራ በዝቶባቸው ዋሉ።

 

በምሽት ተልከው የሄዱት ሰዎች የሚያሰሟቸውን ዘገባ ለማዳመጥ ሁሉም ተሰበሰቡ። ብዙ ሰዎች ቃሉን ሰምተው በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ። ሰይጣንንም ክደው ንስሐ ገቡ። እንዴት ያለ ደስታ ጊዜ ነበር? በመጨረሻም፣ ቡናችንን ጠጥተን ሁላችንም ወደየቤታችን ሄድን። በሚቀጥሉት ቀናት፣ አቶ ቶማ እና እኔ በሁምቦ፣ በኮቴና በሌሎችም አያሌ ቦታዎች ቤተ ክርስቲያንን መሠረትን። በማቴዎስ 28፡ 18-29፣ “ሥልጣን ሁሉ በሰማይና በምድር ተሰጠኝ፣ እንግዲህ ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው። እነሆ፣ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ እኔ ከእናንተ ጋር ነኝ” ያለውን ቃል ለመታዘዝ አጋጣሚ አግኝተን ነበር።           March 2009

Read 600104 times Last modified on Sunday, 13 November 2011 21:48

160356 comments

  • Comment Link DannyswemS Thursday, 09 April 2026 18:21 posted by DannyswemS

    Для оценки состояния используется расширенная диагностика: лабораторные анализы, ЭКГ, психологическое тестирование и биохимические маркеры. По результатам обследования составляется индивидуальный план, включающий детоксикацию, фармакотерапию и реабилитационные мероприятия. Ниже представлена таблица, описывающая структуру этапов лечения.
    Подробнее - запой наркологическая клиника

  • Comment Link SamuelJeste Thursday, 09 April 2026 18:20 posted by SamuelJeste

    Детоксикация — ключевой этап в лечении зависимости. Она направлена на очищение организма от токсинов и нормализацию обмена веществ. В клинике «АстраМед Трезвость» капельницы подбираются индивидуально, с учётом возраста, массы тела и хронических заболеваний пациента. Ниже представлена таблица с основными видами инфузий и их назначением.
    Получить дополнительные сведения - https://narkologicheskaya-klinika-v-astrakhani18.ru/narkologiya-astrakhan-adres

  • Comment Link BrandonGroox Thursday, 09 April 2026 18:18 posted by BrandonGroox

    Безопасность — это не лозунг, а набор решений. Мы избегаем «жёстких» седативных доз, которые создают видимость улучшения и повышают риск скрытых осложнений. Наращивание темпа инфузии происходит постепенно и увязано с динамикой симптомов и цифрами измерений. Любой шаг объясняется пациенту и семье: зачем он выбран, что считается нормальной волной улучшения, в какой момент нужно связаться с дежурным. Такой прозрачный формат снимает тревогу и помогает всем участникам действовать согласованно.
    Ознакомиться с деталями - https://narkolog-na-dom-ivanteevka8.ru/narkolog-na-dom-anonimno-v-ivanteevke/

  • Comment Link Philipslono Thursday, 09 April 2026 18:14 posted by Philipslono

    На первом приёме нарколог собирает полную клиническую картину: продолжительность зависимости, количество и частоту приёмов спиртного, наличие соматических и психических осложнений. Одновременно выполняются лабораторные тесты: общий анализ крови, биохимия (показатели работы печени и почек), электролиты. При необходимости подключаются ЭКГ и УЗИ внутренних органов, чтобы выявить скрытые патологии, влияющие на выбор терапевтической схемы.
    Получить больше информации - http://lechenie-alkogolizma-arkhangelsk0.ru/lechenie-narkomanii-i-alkogolizma-arkhangelsk/https://lechenie-alkogolizma-arkhangelsk0.ru

  • Comment Link mostbet_dden Thursday, 09 April 2026 18:08 posted by mostbet_dden

    mostbet краш http://mostbet65920.help/

  • Comment Link melbet_qhKa Thursday, 09 April 2026 18:01 posted by melbet_qhKa

    melbet пополнить баланс melbet63810.help

  • Comment Link Josephhog Thursday, 09 April 2026 18:00 posted by Josephhog

    Комплексный подход позволяет не просто стабилизировать физическое состояние пациента, но и обеспечить долговременный результат. Каждый этап лечения сопровождается медицинским наблюдением и корректируется по мере улучшения состояния.
    Получить дополнительную информацию - http://narkologicheskaya-klinika-v-krd19.ru/krasnodar-narkologicheskij-czentr/

  • Comment Link pinup_xwPl Thursday, 09 April 2026 17:56 posted by pinup_xwPl

    pin-up Azərpoçt ilə depozit pin-up Azərpoçt ilə depozit

  • Comment Link WilliamTus Thursday, 09 April 2026 17:45 posted by WilliamTus

    Запой — это не просто затянувшийся прием алкоголя, а острое хроническое отравление организма, сопровождающееся тяжёлыми последствиями для сердца, печени, почек, мозга и нервной системы. Снятие абстинентного синдрома без врачебного контроля может привести к тяжёлым осложнениям: судорогам, делирию, инфаркту, внутренним кровотечениям, резкому скачку давления и даже летальному исходу. Только медицинский специалист способен грамотно оценить состояние пациента, купировать опасные проявления и обеспечить полноценное восстановление организма.
    Детальнее - вывод из запоя в стационаре

  • Comment Link pinup_cvSn Thursday, 09 April 2026 17:39 posted by pinup_cvSn

    pin up lucky jet strategiya pin up lucky jet strategiya

Leave a comment

Make sure you enter all the required information, indicated by an asterisk (*). HTML code is not allowed.