×

Warning

JUser: :_load: Unable to load user with ID: 42
Sunday, 13 November 2011 21:07

ፖለቲካና ሃይማኖት ይቀላቀላሉ Featured

Rate this item
(1 Vote)

ርዕሰአንቀጽ - ልዩ እትም

ፖለቲካና ሃይማኖት ይቀላቀላሉ

ሃይማኖትና ፖለቲካ አይቀላቀሉም ይባላል እንጂ ተነጣጥለው አያውቁም። ሰው ማህበራዊ ፍጡር ነው፤ ፖለቲካም በጋርዮሽ  የሚከናወን የሥልጣን ግንኙነትና አደረጃጀት ነው። ሰው ሃይማኖተኛም ነው፤ ራሱን ወይም ከእርሱ ውጭ ያለን ያመልካል፤ አምላክ የለም በማለቱ አምላኪነቱን ያውጃል። ለነፍሱ ያደረ ፈጣሪውን ያመልካል፤ ለአብዮት ያደረ አብዮት ያመልካል፤ ለሥጋው ያደረ ሥጋና ዓለምን ያመልካል።

ከዕለታት አንድ ቀን በአፄ ኃይለሥላሴ ዘመን ሃይማኖትና መንግሥት ተደጋግፈው በሰላም ይኖሩ ነበር። “ሃይማኖት የግል፣ አገር የጋራ ነው” መርሕ ነበር። በደርግ ዘመን ሃይማኖት ተወገዘ፤ እግዚአብሔር በአዋጅ ታገደ። የምሥራቃውያን ዐመል ብቅ አለ። ወደ ምሥራቅ ተዞረ። መንግሥት ካዘዘልህ ውጭ ወዮልህ መጣ። “እግዚአብሔር ይመስገን” ተከለከለ።

እንደምን አደርክ?

ደህና፣

ቤተሰብ እንዴት ነው?

ደህና፣

ሥራ እንዴት ነው?

ደህና።

አንድ ፈረንሣይ ለጋሲዮን የሚኖሩ ወይዘሮ፣ “እግዚአብሔር ይመስገን” ማለት ስላበዙ፣ ካድሬው በልግጫ፣ “ሴትዮ፣ እግዚአብሔር የሚባል የለም፤ ምን እግዚአብሔር እግዚአብሔር ትያለሽ?” ቢላቸው፣ የማይበገሩ ሴትዮ፣ “ከቤቴ ስወጣ አነጋግሬው የመጣሁትን እንዴት የለም ትለኛለህ?” ብለው አፍ አስይዘዋል።

በሶቭየት መጤ ሃይማኖት አገር ተወረረች። ደም ፈሰሰ፣ መንግሥትና ሃይማኖት ተፋቱ ተባለ። ለፖለቲካ ስላላመቸ ቆይቶ “ሃይማኖት አይለያየንም” መጣ። ወሬው “እኩልነት” “ነፃነት” ሆነ። የመስቀል አደባባይ ፕሮቶኮሉ ተቀየረ፤ ከሊቀመንበሩ በስተቀኝ የቤተክህነት መሪ፣ በስተግራ የመስጊዱ ተሰየሙ። የግል የሚባል ለጊዜው ከሠረ። “ሃይማኖት ለፖለቲካ፣ ፖለቲካ ለሃይማኖት” የሚል ስልት ተቀየሰ። “የየሱስ ቃል አያረጅም” የምትለዋ የስዩም ገብረየስ ዝማሬ በአብዮት ሐዋርያት ተጠልፋ የወቅቱን ረብሻ በጉያዋ ደብቃ ብቅ አለች።

በ1983 ዲሞክራሲ የሚሉት ከምዕራቡ ዓለም ከገንዘብ እርዳታ ጋር ተላከልን። እኛም የምዕራባውያንን ዐመል ተቀበልን። ዲሞክራሲም ግለኛነትን እያገነነ “እኔ እኔ፣ ለኔ ለኔ” እያለ ቁና እየተነፈሰ ደረሰ። ወደ ምዕራብ ተዞረ! “ሃይማኖት የግል ነው” በየግልህ ተባለ። በየቀዬህ በየክልልህ ዛፍ ቢሆን ጥላህን ማምለክ መብትህ ነው ተባለ። የእኩልነትና የነፃነት መጽሐፍ ተደገመ።

በአፄ ኃይለሥላሴና በደርግ፣ እንደ ዘመነ ዲሞክራሲ መምረጥና መመረጥ አልነበረም። ሥልጣን፦ መስሎ ላደረ ሹመት፣ ለተዳፈረና ላቅማማ ሽረት ግዞትና ሞት ነበረ። በቀድሞው ልክ ባይሆንም ዛሬም ይኸ አልጠፋም። አሁን ግን ዲሞክራሲ ተብሏልና መምረጥና መመረጥ የሚለው አሠራር ገበያ ላይ ወጥቶ ፀሐይ እየሞቀ ነው። እዚህ ላይ ነው እንግዲህ ልዩነቱ። ሰው ያለ ተጽዕኖ መምረጥ ከቻለ ስብዕናው ተከበረ፣ ሕልውናው ተዘከረ ማለት ነው። መሪነት ብቃት ላላቸው ሁሉ እንጂ ለጥቂቶች የተሰጠ መብት አይሆንም። ወይም መሪዎች እንድ ግብጽ አማልክት ለዘላለም ተሰይመው ሕዝብ የሚያንቀጠቅጡበት አይሆንም፤ ስለ ታታሪነታቸው፣ የሕዝብ አገልጋይና አደራ ተሸካሚ ስለ መሆናቸው ተጠይቀው ግልጽ መልስ የሚሰጡበት፣ የሚመረጡበት ወይም የሚሻሩበት ሁኔታ የተፈጠረበት ዘመን ነው። ሃይማኖተኞችን በምጸት፦ እዚህ ምን ታደርጋላችሁ? ሄዳችሁ ብትጸልዩ አይሻልም? ሲሉ የነበረ እንዲመረጡ ደጅ ጥናት ከጀመሩ ሰነበተ። ተረስቶ የኖረ ሕዝብ በተፈላጊነቱ ሲኩራራና ሲሽኮረመም ማየት ተስፋ ሰጭ ነው። ቅንጅት በ1997 ምርጫ ዋዜማ የኢትዮጵያ ሕዝብ እንዲጸልይ ማሳሰቡ ሃይማኖተኞችን ማግባባቱ ነበር። የቀድሞው የደርግ መሪ በቀውጢ ሰዓት ክርስቲያኑና እስላሙ በየቤተ አምልኮው አምላኩን እንዲማጸን መማጸናቸው አይረሳንም። የደረሰባቸው ጭንቅ ቀድሞ የተናገሩትን ሁሉ አስረስቶአቸው። ለሶሻሊስት ጓዶቻቸው ግን ይህን የነገሩ አይመስለንም፤ ምክንያቱም ቅድም እንዳመለከትነው እግዚአብሔር ስለሌለ ለማን ይጸልዩ? [እርግጥ ጓዶቹ በየጓዳቸው ጸልየው እንደ ሆነ ማወቅ አንችልም፤ ይህንን የሚያውቅ እግዚአብሔር ብቻ ነው]።

የትላንቱ ፖለቲከኛ ሞት ሳይጠራ [“እናት አገር ወይም ሞት!”] ወይም ሰማይና ምድርን ሳይራገም [ይውደም! ይውደም!] ንግግሩን አይቆርጥም። የዛሬ ዘመን ፖለቲከኛ ግን ዋዛ አይደለም። በየንግግሩ መሃል የእግዚአብሔርን ስም ጣልቃ እያስገባ [ሲመችም ለሙስና እየሰገደ] ያሳርጋል። ከአሜሪካ ፖለቲከኞች ቀድቶ ይሆን? እየቆየ እየቆየ የሚገርም ነገር አይጠፋም። እግዚአብሔርም ተቸገረ እኮ! የሶቭየት ሃይማኖት አገራችን ሲገባ “እግዚአብሔር የለም፣ አገር ለቆ ሄዷል” እንዳልተባልን፤ መንግሥታት ሲንኮታኮቱ ከወደ አሜሪካ ብቅ ብሎ ይሆን? የኛዎቹስ አሥሬ እግዚአብሔርን የሚጣሩ በአዲስ አበባና በዋነኛ ከተሞች የሞላውን የወንጌል አማንያንን ድምጽ ለማግኘት አለማቀዳቸውን ማስተባበል አይቻልም። በአንጻሩ ሃይማኖት ማጥላሊያና ተቀናቃኙን ለማጣጣያ ፍቱን መሣሪያ ሆኗል። ደግማ እሥር ቤት የወረደችው ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ አንድ ሰሞን “ጴንጤ” ነች መባሉ ለሙገሳ ወይም ስለርሷ ሐቁን ለመናገር ሳይሆን ለማዋረድ እንደ ነበር የሚያጠያይቅ አይደለም። ምክንያቱም “ሃይማኖት የግል ነው” ሲባል የሰማነው ድሮውንም ከልብ አልነበረማ።

ከዓመት በፊት የተፈቱት የቀድሞ ጠ/ሚኒስትር የአቶ ታምራት ላይኔ ጉዳይ ሌላኛው ነው። በሙስና ተከሰው ከ 12 ዓመት እሥራት በኋላ በአመክሮ ሲፈቱ በአደባባይ “ፖለቲካ በቃኝ፣ ከእንግዲህ ኢየሱስን አገለግላለሁ” ማለታቸው ብዙ ጥያቄና ወረፋ አድርሶባቸዋል። [“ሙስና”፣ ጥንት “ጉቦ” የምንላት ነች፣ ዛሬ ቀጭን ነጠላ ደርባ ብቅ አለች። ደርግ “መንፈስ” ሲል ረቂቅ ቁሳዊነትን ለመግለጽ እንጂ ከቁስ ውጭ እውነት አለ ማለቱ እንዳልነበረ ሁሉ።] ታዲያ አቶ ታምራት ፖለቲካ በቃኝ ማለታቸው ምናኔም እንደማያስጥላቸው የዘነጉ አይመስለንም። “አለም አቀፍ ፈውስ በፍቅርና በአንድነት” ብለው የጀመሩት “ሚኒስትሪ” ሌላው ቢቀር የፖለቲካ ሂደቶችን ማጤንና ከፖለቲካ መሪዎች ጋር መግባባትን እንደሚጠይቅ አይታጣቸውም። በየሄዱበት “የቀድሞው ጠ/ሚኒስትር” መባላቸው የፖለቲካ ጠባሳ እንደተወ የማይገነዘቡ አይመስለንም። እሰብካለሁ ያሉት ወንጌል፣ ሥር ነቀል ለውጥ የሚያስከትል በመሆኑ ምናልባት ዳግም “ሙስና” ውስጥ አልገኝም፣ ከሚያባልግ ሥልጣን እቆጠባለሁ ማለታቸው ይሆናል። ወይም ክርስቶስ ይቅር ብሎኛል እኔም እንደ ዘኬዎስ ማህበራዊ በደሌን አስተካክላለሁ፣ አካክሳለሁ ማለታቸው ይሆናል [ሉቃስ19፡1-10]። ክርስቶስን ሳያውቁ የኖሩትን  ሕይወት ባዶነት ከተረዱስ፣ ኢየሱስ ሕያውና እውነተኛ ጌታ እንደ ሆነ ካመኑ፣ ያለፉበትን የትግልና የሥልጣን ዘመን ከቀመሱት አዲስ ሕይወት አንጻር እውነቱን በመጽሐፍ የማስፈር ብሔራዊ፣ ሰብአዊና የታሪክ ግዴታ እንዳለባቸው እናሳስባለን። ለማንኛውም አንድ ጸሐፊ ወደ ክርስቶስ ማህበር መቀላቀላቸውን አስመልክቶ “ፖለቲከኛ ሲያረጅ፣ ሰባኪ ይሆናል” ብሎ  በከረመ ቁጣና በጥርጣሬ ተችቶአቸዋል። እግዚአብሔርን ማሰብ በስተርጅና ወደ ሞት መቃረቢያ ላይ ነው ማለቱ ይሆን? ምስክርነታቸውን ልብ ብሎ ለሰማ ግን ወንድም ታምራት እውነተኛ የሕይወት ለውጥ እንዳገኙ አያጠራጥርም። የቀረውን ጊዜ ይገልጠዋል። የጠቀስነው ጸሐፊ የክርስቶስን ወንጌል ኃይልና ምሥጢር ካለማወቅ የተነሳ እዚህ ድምዳሜ ላይ ደርሶ ይሆናል ብለን አልፈነዋል።

በሚያዝያ ወር ላይ ከላሊበላ ወሎ ተመራጭ የሆኑት ፖለቲከኛ አቶ ልደቱ አያሌው “ጴንጤ” ሆኑ ተብሎ አገር ታመሰ። “ብሮስታንት” ወይም “ጴንጤ” ሆኑ ብለው ያሟቸው ምን ማለታቸው እንደ ሆነ አላብራሩም። ይኸ “ብሮስታንትና ጴንጤ” በደፈናው መኾን የሌለበት፣ እንደ ለምጥ የሚሸሽ ነገር ይመስላል። “ጴንጤ” ሲፈለግ ማስፈራርያ ሲፈለግም ማግባብያ ነው። አቶ ልደቱን፦ “ጴንጤ ነዎት ይባላል፣ ጴንጤ ነዎት?” ሳይሆን “በኢየሱስ ክርስቶስ ያምናሉ?” ማለት ልኩ ነበር። ለማለት አልን እንጂ ስለ ልኩ የሚገደው ማን ነው? እርሳቸውም ሲመልሱ፣ ስሜን ለማጥፋት ባላንጣ የነዛብኝ እንጂ እኔስ “ጴንጤ” አይደለሁም፣ ሃይማኖቴን አልለወጥኩም እያሉ ነው። ቀድሞውኑ የያዙት ክርስቶስን ከሆነ ሃይማኖታቸውን አጸኑ እንጂ አልለወጡም። ታሪክ ራሱን ይደግማል። አፄ ኃይለሥላሴም እንደዚሁ የወሎውን ልጅ ኢያሱን ሰለሙ ብለው በቤተክህነት ትብብር ሕዝብ እንዳስነሱባቸው ታሪክ ነግሮናል። መቸ ይሆን የሃይማኖት መሪዎች ለኑሮአቸውና ለሥልጣን ሲሉ ከምድራዊ ሥልጣናት ጋር መመሳጠር የሚያቆሙ? የፖለቲካ መሪዎችስ መቸ ይሆን ሳይጦሙ ጦም ማወጅ የሚያቆሙ?

ለመሆኑ፣ ሃይማኖትና ፖለቲካ አይቀላቀሉም የሚለው አስተሳሰብ ከወዴት መጣ? በመጀመሪያ ፖለቲካ ምን እንደ ሆነ ካለማወቅ ነው። ወይም በተሳሳተ መንገድ ከመረዳት ነው። ፖለቲካ መጥፎ፣ ቅጥፈት የሞላበት ጉዳይ ነው ከማለት፤ [ይህም በአንድ መልኩ ትክክል ነው።] ለነፍሱ ያደረና ወንጌል ያነበበ ሰው ከእንደዚህ ዓይነት ምግባር መራቅ  ይኖርበታል ከማለት። ፓለቲካ ግን ከላይ እንደ ጠቀስነው በቅድመ አሳቡ የመንግሥት ሥርዓትና አስተዳደር ነው፤ በክፉዎች እጅ ለክፉ፣ በቅኖች እጅ ለበጎ ሊውል ይችላል። ቀጥሎ፣ የሃይማኖትን ምንነት ካለመረዳት ነው። ሃይማኖት ሲባል ለሰማይ መንግሥት መዘጋጃ ሥጋን ለማጎሳቆያ እንጂ የምድሩን ለመመርመሪያና ታግሎ ኑሮን ለማሸነፊያ እንዳልሆነ ይታሰባል። ይኸ ነው አብዮተኛውን ትውልድ ዙሪያ ገባውን የነገሠውን ድህነት፣ ድንቁርናና የፍትሕ መጓደል አይቶ ሃይማኖትን ለመጥላትና ቤተክርስቲያንን ለማሳደድ ያነሳሳው። እንግዲህ ፖለቲካዬን የሚል ፖለቲካው ውስጥ ይገባል፤ ሃይማኖቴን የሚል ደግሞ እንደየሃይማኖቱ ይሆናል ማለት ይመስላል። ሃይማኖተኛ ትርፍ ሲያይ ፖለቲካውን ይያያዘዋል። ፖለቲከኛም ሲከስር ወይም መከራ ሲበዛበት ሃይማኖተኛ ይሆናል። በዚህ ስሌት ሁለቱ እንደ ዘይትና ውሃ ናቸው፣ አይቀላቀሉም፤ ፖለቲካም እንደ ኮሬንቲ ነው፣ አይቀረብም።

ወንጌል ግን ምን ይላል? ላመኑ “የምድር ጨው ናችሁ” ይላቸዋል። ማህበረሰብ የሞራል ቅንቅን ቦርቡሮ እንዳያፈርሰው ተሳትፎአችሁ አስፈላጊ ነው ይላል። “የዓለም ብርሃን ናችሁ” ይላል። ዓለም ጨለማ ነች፤ እውነትን ከሐሰት መለየት እንዳይጠፋ ብርሃን የሆነውን፣ ጻድቅ ፈራጅ የሆነውን፣ የሰላም አለቃ የሆነውን ኢየሱስን ለማወጅ ታስፈልጋላችሁ። ፈርሃ እግዚአብሔር ሠርጾ እንዲወጣ ምልክት ናችሁ ይላል። ለመሪዎች ጸልዩ፣ ፍትሕ እንዳያጓድሉ፤ በአምላክ አምሳል የተፈጠረውን እንዳይንቁ እንዳያጠቁ፣ ምድርን እንዳያራቁቱ፣ ራሳቸውን እንዳያተልቁ። “ክንዳችን ይህን ሠራችልን” እንዳይሉ።

         

ግንቦት 15/2002 የሕዝብ ምርጫ ይደረጋል። ክርስቲያኖችም እንደ ተቀረው ሕዝብ ብሔራዊ ግዳጃቸውን ሊወጡ፣ መብታቸውን ሊያስከብሩ ድምጽ በመስጠትና በመቀበል በምርጫው ይሳተፋሉ። ከዚህ አንጻር ሃይማኖትና ፖለቲካ አይቀላቀሉም የሚለው አባባል የተሳሳተ ብቻ ሳይሆን ጎጂ ነው። ግብር መክፈል ፖለቲካ ነው። በጎ አድራጎት ፖለቲካ ነው። መገኘት ራሱ ፖለቲካ ነው። “ኢየሱስ በሁሉም ላይ ጌታ ነው” ማለት ከፖለቲካም ዋና ፖለቲካ ነው። ከዳር የቆምን በመሰሉን ዘመናት ሁሉ የፖለቲካው ተካፋይ እንደ ነበርን መካድ አንችልም። መፈክሩ፣ “ከሁሉም በላይ አብዮቱ” ሲለን፣ የለም ምን ተደርጎ፣

“ኢየሱስ ነው ከሁሉም በላይ

ጌታችን ነው ከሁሉም በላይ

አቻ የሌለው

በምድር በሰማይ”

ያልናቸው ጊዜአት ዛሬም አልተለወጡም። ይኸ በነፍሳችን ተወራርደን የምንኖረው ኑሮ ነው። ሃይማኖትና ፖለቲካ አይነጣጠሉም ስንል ግን ከመንግሥት አስተዳደር አንጻር አባባሉን ልናርም ይገባል። የአንድ አገር ሕዝቦች እምነታቸው አንድ ወጥ ስላይደለ፣ ቅድም እንደጠቀስነው ሰው ክቡርነቱ በጅምላ ሳይሆን በግል በፈጣሪው አምሳል መፈጠሩ ስለሆነ፣ የሃይማኖትና የመንግሥት አደረጃጀትና ተልዕኮ ሊነጣጠሉ ያስፈልጋል። ቤተክርስቲያን ኃይሏና ሥልጣኗ ለግራና ለቀኝ የማይለውን ለነፍስና ለሥጋ ለውጥና ተስፋ የሚያመጣውን ወንጌል ስትሰብክ ነው። የዜጎች እምነት የተለያየ ስለሚሆን የዜግነት መብታቸው ሊጣስ አይገባም። ይህን እንጂ ያንን አምኖ ላለመከተል ነፃነት ሊኖር ይገባል። ሃይማኖቱን በግፊት ሳይሆን በአክብሮት የመለፈፍ መብቱ ሊከበርለት ይገባል። ሃይማኖትና መንግሥት አይደራረሱ ማለት አይቻልም። ሳውዲ በሕግ የእስላም አገር ናት፣ ክርስቲያን መሆን በልምድ እንዳየነው እንደ መብት አይቆጠርም፤ ብዙ አሣር ያስከትላል። ዛምቢያ በሕገ መንግሥት የክርስቲያን አገር ናት፤ እስላም መሆን ግን ለእስር አይዳርግም፤ ዜግነትን አያስነጥቅም። የተቀሩት አገሮች ይህንኑ በተለያየ መልኩ ተግባራዊ እያደረጉ ይገኛሉ። ባጭሩ፣ ሙስሊሞች በክርስቲያን አገር ያላቸውን ነጻነት፣ ክርስቲያኖች በሙስሊም አገር አይኖራቸውም።

እፊታችን ባለው ምርጫ ላይ ለመሳተፍ ምን ጠቃሚ ክርስቲያናዊ መመዘኛዎች ሊኖሩ ይችላሉ? እንግዲህ ዝርዝሩ ላይ አቋማችን ሊለያይ ቢችልም፣ መሠረታዊው ላይ አንድ ነው። መሠረታዊው ምንድነው? የመጀመሪያው፣ የሥልጣን ሁሉ ምንጭና ባለቤት እግዚአብሔር ነው። ቢገነዘቡ ባይገነዘቡ ሥልጣን ላይ ያሉ ሁሉ ሥልጣናቸው በአደራ የተሰጣቸው ነው። መሪዎች የሚሾሙት ጽድቅና ፍትሕን ለማስፈን ነው። በምድሪቱ ሰላም ቢሆን ከእግዚአብሔር ነው፣ የአማንያን ጸሎትና ተሳትፎ ፍሬ ነው። ስደትና መከራ ቢመጣ እግዚአብሔር ለዓላማ ፈቅዶ ነው። ሁሉን የሠራ እግዚአብሔር ነው፤ እግዚአብሔር በሠራው ሰው ሊመሰገን አይገባም። ወንጌልን ያመኑ በሞት ሆነ በሕይወት ከእግዚአብሔር ሌላ ተጨማሪ ምክንያት አያሻቸውም።[ፊል1፡20] አለዚያ በሰላሙ ሰዓት ሰውን ማመስገን፣ በስደት ደግሞ እግዚአብሔርን ማማረር ሊመጣ ነው። ሁለተኛው፣ ሰው ሁሉ በእግዚአብሔር አምሳል ተፈጥሯል የሚል ነው። [1ኛቆሮ11፡7፤ዘፍ1፡27] ሰው ከዝንጀሮ መጣ ወይም ክብሩና ህልውናው የተቃረኑ ማህበራዊ ኃይላት ውጤት ነው የሚል ሁሉ የሳተ ነው። ወይም አንዱን ሰው ወይም ጎሣ ከሌላው ሰው ወይም ጎሣ የሚያበላልጥና የሚያቃቅር አስተሳሰብ ሁሉ የወንጌልን ሥልጣን የሚጻረር ነው። ሦስተኛው ከሁለተኛው የሚቀጥል ነው፤ ይኸውም፣ ሰው በአምላክ አምሳል ተፈጥሯል ካልን፣ የደሆች [የሥራ አጦች፣ የአዛውንት፣ የመንገድ ተዳዳሪ ሕጻናትና ሴቶች] ሁኔታ ምን ይመስላል? መሪዎች የገቡትን ቃል ያጥፋሉ ወይስ ይፈጽማሉ? ሕግ ለሁሉም እኩል ይሠራል? ሰብአዊ መብት [የመደራጀት፣ የመናገርና የመጻፍ] ይከበራል? ክፉ የሚያደርጉ ተመስግነው መልካም የሚያደርጉ ይገፋሉ? በዚህ ሁሉ ቤተ/ክ ምዕመኑን በጽድቅ ወንጌል ማስታጠቅ ትታ ከምድራዊና ጊዜአዊ ድርጅቶችና አስተሳሰቦች ጋር መወዳጀትና መወገን ብትጀምር ሥልጣኗን ትጥላለች፤ ያም ለክርስቶስ ክብር አይሆንም። ጸጋ፣ ችሎታና ጥሪ ያላቸው አማንያን ደግሞ ተመርጠው በፖለቲካም መሳተፍ ይችላሉ።

ከሁሉ በላይ ግን መጸለይ ነው፤ ሰላም እንዲኖር፣ አመጸኞች እንዲገቱ፣ እንዳያይሉ፣ የሰላም ሰዎች፣ ቅን ዜጎች፣ ፍትሕ የሚወዱ እንዲነሱ። ባለጠጎች ደሃውን መኖሪያ እንዳያሳጡት። የተሰጠን የክርስቶስ መንፈስ ስለሆነ እርሱ ወደ እውነት ሁሉ ይመራናል። ሰው የማያየውን ያያል፤ ፖለቲካ የማይመረምረውን ይመረምራል። የእግዚአብሔር መንፈስ ሰው እንደሚያይ አያይም። ሥልጣናትና ኃይላት በስውር የሚመክሩትን ይሰማል፣ ለባሪያዎቹ ያስታውቃል። ቅንነት የተገኘበትን ይገነዘባል፤ መነሻን ብቻ ሳይሆን ፍጻሜን ያያል። ከስምንቱ የእሴይ ልጆች በነቢዩ ሳሙኤል የተመረጠው በሥፍራው ላይ ያልነበረው ትንሹ ዳዊት ነው። እግዚአብሔር እንደ ቂሮስ ያሉትን አሕዛብ ፈቃዱን እንዲፈጽሙ ያስነሳል። ይህን ያነሳል፤ ያንን ይጥላል። ዕጣ በጉያ ይጣላል፣ መደብዋ ግን ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው። ሥልጣን ሁሉ በሰማይና በምድር የእግዚአብሔርና የመሲሑ ነው። እግዚአብሔር ምድራችንን ርህራሄ፣ ቅንነትና ማስተዋል ባላቸው ሰዎች ይባርክልን። [ጥቅሶች፦ ሮሜ 13፡1-5፤ የሐዋ ሥራ 5፡29፤ ራእይ 13፤ 1ኛጴጥሮስ 2፡13-17፤ ማርቆስ 12፡13-17፤ ቲቶ3፡1፤ ምሳሌ16፡33፤ 1ኛሳሙኤል16፤ 2ኛነገሥት 6፡8-13፤ 2ኛ ዜና 36፡22፤ ዕዝራ1፡2፤ ኢሳይያስ 6፡1-]               5/13/2010

 

Read 563818 times

132146 comments

  • Comment Link dconlineims Wednesday, 04 February 2026 05:36 posted by dconlineims

    https://telegra.ph/Samyj-slozhnyj-test-na-iq-Ajkyu-kakoj-dolzhen-byt-Iq-test-dlya-detej-9-let-3-klass-Koehfficient-umstvennogo-razvitiya-iq-naibole-02-03

  • Comment Link yvonlinecqh Wednesday, 04 February 2026 05:34 posted by yvonlinecqh

    https://telegra.ph/Ajkyu-vysokij-skolko-Iq-kakoj-normalnyj-YAvlyaetsya-li-ajkyu-pokazatelem-uma-Srednee-qi-cheloveka-02-03

  • Comment Link buy_oosa Wednesday, 04 February 2026 05:31 posted by buy_oosa

    If you are looking for a convenient way korean lip fillers, visit our website for safe shopping.
    A growing number of individuals choose buying Botox over the internet instead of going to conventional medical practices.

    The possibility to compare various brands and concentrations attracts experienced users. Discreet packaging ensures privacy throughout the entire purchasing process. Experienced users appreciate the ability to evaluate multiple brands and dosages conveniently.

    Authentic Botox must come from licensed distributors with proper documentation. Reputable sellers always provide batch numbers and expiration dates with every shipment. Counterfeit products containing incorrect ingredients pose serious health dangers. Checking for holograms and original Allergan packaging helps verify legitimacy. Genuine Botox should only be sourced from authorized distributors who supply complete documentation.

    Consulting qualified medical professionals before usage remains essential regardless of purchase source. Proper storage conditions during transportation directly influence product effectiveness. Getting advice from certified practitioners prior to usage remains vital regardless of the purchasing method.

    Look for websites displaying clear contact information including physical address and phone number. Reliable vendors usually possess SSL certificates ensuring secure payment processing. Positive feedback across independent review platforms serves as strong indicator of trustworthiness. Search for sites showing transparent contact details such as real office location and telephone contacts.

    Suppliers offering detailed certificates of analysis deserve higher consideration. Avoid sellers demanding only cryptocurrency without alternative payment options. Sellers presenting complete analysis documentation merit increased confidence.

    Current market conditions allow accessing promotional offers almost constantly. Many suppliers now provide subscription models delivering regular shipments automatically. Advanced tracking systems show precise delivery status in real time. Educational resources accompanying orders help first-time users understand proper handling. Present-day conditions permit utilizing ongoing special offers regularly.

    International shipping options expanded dramatically making global access much simpler. Professional customer support teams assist with questions twenty-four hours daily. Global shipping services expanded considerably facilitating cross-border acquisition.

  • Comment Link rjonlineiia Wednesday, 04 February 2026 05:25 posted by rjonlineiia

    https://telegra.ph/Raspredelenie-iq-Koehfficient-intellekta-ehto-ocenka-kolichestvennaya-ili-kachestvennaya-Kak-opredelit-svoj-ajkyu-test-besplatno-02-03

  • Comment Link syonlinewcr Wednesday, 04 February 2026 05:23 posted by syonlinewcr

    https://telegra.ph/Iq-test-bystro-Test-na-ajkyu-dlya-18-let-Skolko-maksimum-ajkyu-u-cheloveka-Test-na-ajkyu-besplatno-korotkij-02-03

  • Comment Link kanatnye_raon Wednesday, 04 February 2026 05:21 posted by kanatnye_raon

    Для безопасной и эффективной работы на высоте выбирайте монтаж мачтовых подъемников, доступные с доставкой по России.
    Надежность и безопасность во время работы — основные характеристики таких подъемников.

  • Comment Link nozhnichny_ixSt Wednesday, 04 February 2026 05:16 posted by nozhnichny_ixSt

    Для безопасной и эффективной работы на высоте рекомендуем ознакомиться с ассортиментом грузовой ножничный подъемник, который идеально подойдёт для ваших задач.
    Грузоподъемность и высота подъема ножничных подъемников варьируется в зависимости от модели и назначения.

    Уникальный механизм перекрещенных рычагов в ножничных подъемникахгарантирует безопасность и комфорт при подъеме.

  • Comment Link cvonlinemqk Wednesday, 04 February 2026 05:14 posted by cvonlinemqk

    https://telegra.ph/Normy-iq-po-vozrastam-Ajkyu-test-25-voprosov-Opredelenie-urovnya-intellekta-Iq-85-02-03

  • Comment Link ouonlinehue Wednesday, 04 February 2026 05:13 posted by ouonlinehue

    https://telegra.ph/Skolko-v-srednem-dolzhno-byt-iq-u-cheloveka-Test-iw-Iq-test-originalnyj-Kakoj-maksimalnyj-ajkyu-mozhet-byt-02-03

  • Comment Link podemnoe_dqei Wednesday, 04 February 2026 05:11 posted by podemnoe_dqei

    Для повышения эффективности работы на складе рекомендуем обратить внимание на грузовой подъемник санкт петербург, который обеспечит безопасное и надежное перемещение грузов.
    Каждый из этих видов предназначен для выполнения специфических задач.

Leave a comment

Make sure you enter all the required information, indicated by an asterisk (*). HTML code is not allowed.