×

Warning

JUser: :_load: Unable to load user with ID: 42
Sunday, 13 November 2011 21:07

ፖለቲካና ሃይማኖት ይቀላቀላሉ Featured

Rate this item
(1 Vote)

ርዕሰአንቀጽ - ልዩ እትም

ፖለቲካና ሃይማኖት ይቀላቀላሉ

ሃይማኖትና ፖለቲካ አይቀላቀሉም ይባላል እንጂ ተነጣጥለው አያውቁም። ሰው ማህበራዊ ፍጡር ነው፤ ፖለቲካም በጋርዮሽ  የሚከናወን የሥልጣን ግንኙነትና አደረጃጀት ነው። ሰው ሃይማኖተኛም ነው፤ ራሱን ወይም ከእርሱ ውጭ ያለን ያመልካል፤ አምላክ የለም በማለቱ አምላኪነቱን ያውጃል። ለነፍሱ ያደረ ፈጣሪውን ያመልካል፤ ለአብዮት ያደረ አብዮት ያመልካል፤ ለሥጋው ያደረ ሥጋና ዓለምን ያመልካል።

ከዕለታት አንድ ቀን በአፄ ኃይለሥላሴ ዘመን ሃይማኖትና መንግሥት ተደጋግፈው በሰላም ይኖሩ ነበር። “ሃይማኖት የግል፣ አገር የጋራ ነው” መርሕ ነበር። በደርግ ዘመን ሃይማኖት ተወገዘ፤ እግዚአብሔር በአዋጅ ታገደ። የምሥራቃውያን ዐመል ብቅ አለ። ወደ ምሥራቅ ተዞረ። መንግሥት ካዘዘልህ ውጭ ወዮልህ መጣ። “እግዚአብሔር ይመስገን” ተከለከለ።

እንደምን አደርክ?

ደህና፣

ቤተሰብ እንዴት ነው?

ደህና፣

ሥራ እንዴት ነው?

ደህና።

አንድ ፈረንሣይ ለጋሲዮን የሚኖሩ ወይዘሮ፣ “እግዚአብሔር ይመስገን” ማለት ስላበዙ፣ ካድሬው በልግጫ፣ “ሴትዮ፣ እግዚአብሔር የሚባል የለም፤ ምን እግዚአብሔር እግዚአብሔር ትያለሽ?” ቢላቸው፣ የማይበገሩ ሴትዮ፣ “ከቤቴ ስወጣ አነጋግሬው የመጣሁትን እንዴት የለም ትለኛለህ?” ብለው አፍ አስይዘዋል።

በሶቭየት መጤ ሃይማኖት አገር ተወረረች። ደም ፈሰሰ፣ መንግሥትና ሃይማኖት ተፋቱ ተባለ። ለፖለቲካ ስላላመቸ ቆይቶ “ሃይማኖት አይለያየንም” መጣ። ወሬው “እኩልነት” “ነፃነት” ሆነ። የመስቀል አደባባይ ፕሮቶኮሉ ተቀየረ፤ ከሊቀመንበሩ በስተቀኝ የቤተክህነት መሪ፣ በስተግራ የመስጊዱ ተሰየሙ። የግል የሚባል ለጊዜው ከሠረ። “ሃይማኖት ለፖለቲካ፣ ፖለቲካ ለሃይማኖት” የሚል ስልት ተቀየሰ። “የየሱስ ቃል አያረጅም” የምትለዋ የስዩም ገብረየስ ዝማሬ በአብዮት ሐዋርያት ተጠልፋ የወቅቱን ረብሻ በጉያዋ ደብቃ ብቅ አለች።

በ1983 ዲሞክራሲ የሚሉት ከምዕራቡ ዓለም ከገንዘብ እርዳታ ጋር ተላከልን። እኛም የምዕራባውያንን ዐመል ተቀበልን። ዲሞክራሲም ግለኛነትን እያገነነ “እኔ እኔ፣ ለኔ ለኔ” እያለ ቁና እየተነፈሰ ደረሰ። ወደ ምዕራብ ተዞረ! “ሃይማኖት የግል ነው” በየግልህ ተባለ። በየቀዬህ በየክልልህ ዛፍ ቢሆን ጥላህን ማምለክ መብትህ ነው ተባለ። የእኩልነትና የነፃነት መጽሐፍ ተደገመ።

በአፄ ኃይለሥላሴና በደርግ፣ እንደ ዘመነ ዲሞክራሲ መምረጥና መመረጥ አልነበረም። ሥልጣን፦ መስሎ ላደረ ሹመት፣ ለተዳፈረና ላቅማማ ሽረት ግዞትና ሞት ነበረ። በቀድሞው ልክ ባይሆንም ዛሬም ይኸ አልጠፋም። አሁን ግን ዲሞክራሲ ተብሏልና መምረጥና መመረጥ የሚለው አሠራር ገበያ ላይ ወጥቶ ፀሐይ እየሞቀ ነው። እዚህ ላይ ነው እንግዲህ ልዩነቱ። ሰው ያለ ተጽዕኖ መምረጥ ከቻለ ስብዕናው ተከበረ፣ ሕልውናው ተዘከረ ማለት ነው። መሪነት ብቃት ላላቸው ሁሉ እንጂ ለጥቂቶች የተሰጠ መብት አይሆንም። ወይም መሪዎች እንድ ግብጽ አማልክት ለዘላለም ተሰይመው ሕዝብ የሚያንቀጠቅጡበት አይሆንም፤ ስለ ታታሪነታቸው፣ የሕዝብ አገልጋይና አደራ ተሸካሚ ስለ መሆናቸው ተጠይቀው ግልጽ መልስ የሚሰጡበት፣ የሚመረጡበት ወይም የሚሻሩበት ሁኔታ የተፈጠረበት ዘመን ነው። ሃይማኖተኞችን በምጸት፦ እዚህ ምን ታደርጋላችሁ? ሄዳችሁ ብትጸልዩ አይሻልም? ሲሉ የነበረ እንዲመረጡ ደጅ ጥናት ከጀመሩ ሰነበተ። ተረስቶ የኖረ ሕዝብ በተፈላጊነቱ ሲኩራራና ሲሽኮረመም ማየት ተስፋ ሰጭ ነው። ቅንጅት በ1997 ምርጫ ዋዜማ የኢትዮጵያ ሕዝብ እንዲጸልይ ማሳሰቡ ሃይማኖተኞችን ማግባባቱ ነበር። የቀድሞው የደርግ መሪ በቀውጢ ሰዓት ክርስቲያኑና እስላሙ በየቤተ አምልኮው አምላኩን እንዲማጸን መማጸናቸው አይረሳንም። የደረሰባቸው ጭንቅ ቀድሞ የተናገሩትን ሁሉ አስረስቶአቸው። ለሶሻሊስት ጓዶቻቸው ግን ይህን የነገሩ አይመስለንም፤ ምክንያቱም ቅድም እንዳመለከትነው እግዚአብሔር ስለሌለ ለማን ይጸልዩ? [እርግጥ ጓዶቹ በየጓዳቸው ጸልየው እንደ ሆነ ማወቅ አንችልም፤ ይህንን የሚያውቅ እግዚአብሔር ብቻ ነው]።

የትላንቱ ፖለቲከኛ ሞት ሳይጠራ [“እናት አገር ወይም ሞት!”] ወይም ሰማይና ምድርን ሳይራገም [ይውደም! ይውደም!] ንግግሩን አይቆርጥም። የዛሬ ዘመን ፖለቲከኛ ግን ዋዛ አይደለም። በየንግግሩ መሃል የእግዚአብሔርን ስም ጣልቃ እያስገባ [ሲመችም ለሙስና እየሰገደ] ያሳርጋል። ከአሜሪካ ፖለቲከኞች ቀድቶ ይሆን? እየቆየ እየቆየ የሚገርም ነገር አይጠፋም። እግዚአብሔርም ተቸገረ እኮ! የሶቭየት ሃይማኖት አገራችን ሲገባ “እግዚአብሔር የለም፣ አገር ለቆ ሄዷል” እንዳልተባልን፤ መንግሥታት ሲንኮታኮቱ ከወደ አሜሪካ ብቅ ብሎ ይሆን? የኛዎቹስ አሥሬ እግዚአብሔርን የሚጣሩ በአዲስ አበባና በዋነኛ ከተሞች የሞላውን የወንጌል አማንያንን ድምጽ ለማግኘት አለማቀዳቸውን ማስተባበል አይቻልም። በአንጻሩ ሃይማኖት ማጥላሊያና ተቀናቃኙን ለማጣጣያ ፍቱን መሣሪያ ሆኗል። ደግማ እሥር ቤት የወረደችው ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ አንድ ሰሞን “ጴንጤ” ነች መባሉ ለሙገሳ ወይም ስለርሷ ሐቁን ለመናገር ሳይሆን ለማዋረድ እንደ ነበር የሚያጠያይቅ አይደለም። ምክንያቱም “ሃይማኖት የግል ነው” ሲባል የሰማነው ድሮውንም ከልብ አልነበረማ።

ከዓመት በፊት የተፈቱት የቀድሞ ጠ/ሚኒስትር የአቶ ታምራት ላይኔ ጉዳይ ሌላኛው ነው። በሙስና ተከሰው ከ 12 ዓመት እሥራት በኋላ በአመክሮ ሲፈቱ በአደባባይ “ፖለቲካ በቃኝ፣ ከእንግዲህ ኢየሱስን አገለግላለሁ” ማለታቸው ብዙ ጥያቄና ወረፋ አድርሶባቸዋል። [“ሙስና”፣ ጥንት “ጉቦ” የምንላት ነች፣ ዛሬ ቀጭን ነጠላ ደርባ ብቅ አለች። ደርግ “መንፈስ” ሲል ረቂቅ ቁሳዊነትን ለመግለጽ እንጂ ከቁስ ውጭ እውነት አለ ማለቱ እንዳልነበረ ሁሉ።] ታዲያ አቶ ታምራት ፖለቲካ በቃኝ ማለታቸው ምናኔም እንደማያስጥላቸው የዘነጉ አይመስለንም። “አለም አቀፍ ፈውስ በፍቅርና በአንድነት” ብለው የጀመሩት “ሚኒስትሪ” ሌላው ቢቀር የፖለቲካ ሂደቶችን ማጤንና ከፖለቲካ መሪዎች ጋር መግባባትን እንደሚጠይቅ አይታጣቸውም። በየሄዱበት “የቀድሞው ጠ/ሚኒስትር” መባላቸው የፖለቲካ ጠባሳ እንደተወ የማይገነዘቡ አይመስለንም። እሰብካለሁ ያሉት ወንጌል፣ ሥር ነቀል ለውጥ የሚያስከትል በመሆኑ ምናልባት ዳግም “ሙስና” ውስጥ አልገኝም፣ ከሚያባልግ ሥልጣን እቆጠባለሁ ማለታቸው ይሆናል። ወይም ክርስቶስ ይቅር ብሎኛል እኔም እንደ ዘኬዎስ ማህበራዊ በደሌን አስተካክላለሁ፣ አካክሳለሁ ማለታቸው ይሆናል [ሉቃስ19፡1-10]። ክርስቶስን ሳያውቁ የኖሩትን  ሕይወት ባዶነት ከተረዱስ፣ ኢየሱስ ሕያውና እውነተኛ ጌታ እንደ ሆነ ካመኑ፣ ያለፉበትን የትግልና የሥልጣን ዘመን ከቀመሱት አዲስ ሕይወት አንጻር እውነቱን በመጽሐፍ የማስፈር ብሔራዊ፣ ሰብአዊና የታሪክ ግዴታ እንዳለባቸው እናሳስባለን። ለማንኛውም አንድ ጸሐፊ ወደ ክርስቶስ ማህበር መቀላቀላቸውን አስመልክቶ “ፖለቲከኛ ሲያረጅ፣ ሰባኪ ይሆናል” ብሎ  በከረመ ቁጣና በጥርጣሬ ተችቶአቸዋል። እግዚአብሔርን ማሰብ በስተርጅና ወደ ሞት መቃረቢያ ላይ ነው ማለቱ ይሆን? ምስክርነታቸውን ልብ ብሎ ለሰማ ግን ወንድም ታምራት እውነተኛ የሕይወት ለውጥ እንዳገኙ አያጠራጥርም። የቀረውን ጊዜ ይገልጠዋል። የጠቀስነው ጸሐፊ የክርስቶስን ወንጌል ኃይልና ምሥጢር ካለማወቅ የተነሳ እዚህ ድምዳሜ ላይ ደርሶ ይሆናል ብለን አልፈነዋል።

በሚያዝያ ወር ላይ ከላሊበላ ወሎ ተመራጭ የሆኑት ፖለቲከኛ አቶ ልደቱ አያሌው “ጴንጤ” ሆኑ ተብሎ አገር ታመሰ። “ብሮስታንት” ወይም “ጴንጤ” ሆኑ ብለው ያሟቸው ምን ማለታቸው እንደ ሆነ አላብራሩም። ይኸ “ብሮስታንትና ጴንጤ” በደፈናው መኾን የሌለበት፣ እንደ ለምጥ የሚሸሽ ነገር ይመስላል። “ጴንጤ” ሲፈለግ ማስፈራርያ ሲፈለግም ማግባብያ ነው። አቶ ልደቱን፦ “ጴንጤ ነዎት ይባላል፣ ጴንጤ ነዎት?” ሳይሆን “በኢየሱስ ክርስቶስ ያምናሉ?” ማለት ልኩ ነበር። ለማለት አልን እንጂ ስለ ልኩ የሚገደው ማን ነው? እርሳቸውም ሲመልሱ፣ ስሜን ለማጥፋት ባላንጣ የነዛብኝ እንጂ እኔስ “ጴንጤ” አይደለሁም፣ ሃይማኖቴን አልለወጥኩም እያሉ ነው። ቀድሞውኑ የያዙት ክርስቶስን ከሆነ ሃይማኖታቸውን አጸኑ እንጂ አልለወጡም። ታሪክ ራሱን ይደግማል። አፄ ኃይለሥላሴም እንደዚሁ የወሎውን ልጅ ኢያሱን ሰለሙ ብለው በቤተክህነት ትብብር ሕዝብ እንዳስነሱባቸው ታሪክ ነግሮናል። መቸ ይሆን የሃይማኖት መሪዎች ለኑሮአቸውና ለሥልጣን ሲሉ ከምድራዊ ሥልጣናት ጋር መመሳጠር የሚያቆሙ? የፖለቲካ መሪዎችስ መቸ ይሆን ሳይጦሙ ጦም ማወጅ የሚያቆሙ?

ለመሆኑ፣ ሃይማኖትና ፖለቲካ አይቀላቀሉም የሚለው አስተሳሰብ ከወዴት መጣ? በመጀመሪያ ፖለቲካ ምን እንደ ሆነ ካለማወቅ ነው። ወይም በተሳሳተ መንገድ ከመረዳት ነው። ፖለቲካ መጥፎ፣ ቅጥፈት የሞላበት ጉዳይ ነው ከማለት፤ [ይህም በአንድ መልኩ ትክክል ነው።] ለነፍሱ ያደረና ወንጌል ያነበበ ሰው ከእንደዚህ ዓይነት ምግባር መራቅ  ይኖርበታል ከማለት። ፓለቲካ ግን ከላይ እንደ ጠቀስነው በቅድመ አሳቡ የመንግሥት ሥርዓትና አስተዳደር ነው፤ በክፉዎች እጅ ለክፉ፣ በቅኖች እጅ ለበጎ ሊውል ይችላል። ቀጥሎ፣ የሃይማኖትን ምንነት ካለመረዳት ነው። ሃይማኖት ሲባል ለሰማይ መንግሥት መዘጋጃ ሥጋን ለማጎሳቆያ እንጂ የምድሩን ለመመርመሪያና ታግሎ ኑሮን ለማሸነፊያ እንዳልሆነ ይታሰባል። ይኸ ነው አብዮተኛውን ትውልድ ዙሪያ ገባውን የነገሠውን ድህነት፣ ድንቁርናና የፍትሕ መጓደል አይቶ ሃይማኖትን ለመጥላትና ቤተክርስቲያንን ለማሳደድ ያነሳሳው። እንግዲህ ፖለቲካዬን የሚል ፖለቲካው ውስጥ ይገባል፤ ሃይማኖቴን የሚል ደግሞ እንደየሃይማኖቱ ይሆናል ማለት ይመስላል። ሃይማኖተኛ ትርፍ ሲያይ ፖለቲካውን ይያያዘዋል። ፖለቲከኛም ሲከስር ወይም መከራ ሲበዛበት ሃይማኖተኛ ይሆናል። በዚህ ስሌት ሁለቱ እንደ ዘይትና ውሃ ናቸው፣ አይቀላቀሉም፤ ፖለቲካም እንደ ኮሬንቲ ነው፣ አይቀረብም።

ወንጌል ግን ምን ይላል? ላመኑ “የምድር ጨው ናችሁ” ይላቸዋል። ማህበረሰብ የሞራል ቅንቅን ቦርቡሮ እንዳያፈርሰው ተሳትፎአችሁ አስፈላጊ ነው ይላል። “የዓለም ብርሃን ናችሁ” ይላል። ዓለም ጨለማ ነች፤ እውነትን ከሐሰት መለየት እንዳይጠፋ ብርሃን የሆነውን፣ ጻድቅ ፈራጅ የሆነውን፣ የሰላም አለቃ የሆነውን ኢየሱስን ለማወጅ ታስፈልጋላችሁ። ፈርሃ እግዚአብሔር ሠርጾ እንዲወጣ ምልክት ናችሁ ይላል። ለመሪዎች ጸልዩ፣ ፍትሕ እንዳያጓድሉ፤ በአምላክ አምሳል የተፈጠረውን እንዳይንቁ እንዳያጠቁ፣ ምድርን እንዳያራቁቱ፣ ራሳቸውን እንዳያተልቁ። “ክንዳችን ይህን ሠራችልን” እንዳይሉ።

         

ግንቦት 15/2002 የሕዝብ ምርጫ ይደረጋል። ክርስቲያኖችም እንደ ተቀረው ሕዝብ ብሔራዊ ግዳጃቸውን ሊወጡ፣ መብታቸውን ሊያስከብሩ ድምጽ በመስጠትና በመቀበል በምርጫው ይሳተፋሉ። ከዚህ አንጻር ሃይማኖትና ፖለቲካ አይቀላቀሉም የሚለው አባባል የተሳሳተ ብቻ ሳይሆን ጎጂ ነው። ግብር መክፈል ፖለቲካ ነው። በጎ አድራጎት ፖለቲካ ነው። መገኘት ራሱ ፖለቲካ ነው። “ኢየሱስ በሁሉም ላይ ጌታ ነው” ማለት ከፖለቲካም ዋና ፖለቲካ ነው። ከዳር የቆምን በመሰሉን ዘመናት ሁሉ የፖለቲካው ተካፋይ እንደ ነበርን መካድ አንችልም። መፈክሩ፣ “ከሁሉም በላይ አብዮቱ” ሲለን፣ የለም ምን ተደርጎ፣

“ኢየሱስ ነው ከሁሉም በላይ

ጌታችን ነው ከሁሉም በላይ

አቻ የሌለው

በምድር በሰማይ”

ያልናቸው ጊዜአት ዛሬም አልተለወጡም። ይኸ በነፍሳችን ተወራርደን የምንኖረው ኑሮ ነው። ሃይማኖትና ፖለቲካ አይነጣጠሉም ስንል ግን ከመንግሥት አስተዳደር አንጻር አባባሉን ልናርም ይገባል። የአንድ አገር ሕዝቦች እምነታቸው አንድ ወጥ ስላይደለ፣ ቅድም እንደጠቀስነው ሰው ክቡርነቱ በጅምላ ሳይሆን በግል በፈጣሪው አምሳል መፈጠሩ ስለሆነ፣ የሃይማኖትና የመንግሥት አደረጃጀትና ተልዕኮ ሊነጣጠሉ ያስፈልጋል። ቤተክርስቲያን ኃይሏና ሥልጣኗ ለግራና ለቀኝ የማይለውን ለነፍስና ለሥጋ ለውጥና ተስፋ የሚያመጣውን ወንጌል ስትሰብክ ነው። የዜጎች እምነት የተለያየ ስለሚሆን የዜግነት መብታቸው ሊጣስ አይገባም። ይህን እንጂ ያንን አምኖ ላለመከተል ነፃነት ሊኖር ይገባል። ሃይማኖቱን በግፊት ሳይሆን በአክብሮት የመለፈፍ መብቱ ሊከበርለት ይገባል። ሃይማኖትና መንግሥት አይደራረሱ ማለት አይቻልም። ሳውዲ በሕግ የእስላም አገር ናት፣ ክርስቲያን መሆን በልምድ እንዳየነው እንደ መብት አይቆጠርም፤ ብዙ አሣር ያስከትላል። ዛምቢያ በሕገ መንግሥት የክርስቲያን አገር ናት፤ እስላም መሆን ግን ለእስር አይዳርግም፤ ዜግነትን አያስነጥቅም። የተቀሩት አገሮች ይህንኑ በተለያየ መልኩ ተግባራዊ እያደረጉ ይገኛሉ። ባጭሩ፣ ሙስሊሞች በክርስቲያን አገር ያላቸውን ነጻነት፣ ክርስቲያኖች በሙስሊም አገር አይኖራቸውም።

እፊታችን ባለው ምርጫ ላይ ለመሳተፍ ምን ጠቃሚ ክርስቲያናዊ መመዘኛዎች ሊኖሩ ይችላሉ? እንግዲህ ዝርዝሩ ላይ አቋማችን ሊለያይ ቢችልም፣ መሠረታዊው ላይ አንድ ነው። መሠረታዊው ምንድነው? የመጀመሪያው፣ የሥልጣን ሁሉ ምንጭና ባለቤት እግዚአብሔር ነው። ቢገነዘቡ ባይገነዘቡ ሥልጣን ላይ ያሉ ሁሉ ሥልጣናቸው በአደራ የተሰጣቸው ነው። መሪዎች የሚሾሙት ጽድቅና ፍትሕን ለማስፈን ነው። በምድሪቱ ሰላም ቢሆን ከእግዚአብሔር ነው፣ የአማንያን ጸሎትና ተሳትፎ ፍሬ ነው። ስደትና መከራ ቢመጣ እግዚአብሔር ለዓላማ ፈቅዶ ነው። ሁሉን የሠራ እግዚአብሔር ነው፤ እግዚአብሔር በሠራው ሰው ሊመሰገን አይገባም። ወንጌልን ያመኑ በሞት ሆነ በሕይወት ከእግዚአብሔር ሌላ ተጨማሪ ምክንያት አያሻቸውም።[ፊል1፡20] አለዚያ በሰላሙ ሰዓት ሰውን ማመስገን፣ በስደት ደግሞ እግዚአብሔርን ማማረር ሊመጣ ነው። ሁለተኛው፣ ሰው ሁሉ በእግዚአብሔር አምሳል ተፈጥሯል የሚል ነው። [1ኛቆሮ11፡7፤ዘፍ1፡27] ሰው ከዝንጀሮ መጣ ወይም ክብሩና ህልውናው የተቃረኑ ማህበራዊ ኃይላት ውጤት ነው የሚል ሁሉ የሳተ ነው። ወይም አንዱን ሰው ወይም ጎሣ ከሌላው ሰው ወይም ጎሣ የሚያበላልጥና የሚያቃቅር አስተሳሰብ ሁሉ የወንጌልን ሥልጣን የሚጻረር ነው። ሦስተኛው ከሁለተኛው የሚቀጥል ነው፤ ይኸውም፣ ሰው በአምላክ አምሳል ተፈጥሯል ካልን፣ የደሆች [የሥራ አጦች፣ የአዛውንት፣ የመንገድ ተዳዳሪ ሕጻናትና ሴቶች] ሁኔታ ምን ይመስላል? መሪዎች የገቡትን ቃል ያጥፋሉ ወይስ ይፈጽማሉ? ሕግ ለሁሉም እኩል ይሠራል? ሰብአዊ መብት [የመደራጀት፣ የመናገርና የመጻፍ] ይከበራል? ክፉ የሚያደርጉ ተመስግነው መልካም የሚያደርጉ ይገፋሉ? በዚህ ሁሉ ቤተ/ክ ምዕመኑን በጽድቅ ወንጌል ማስታጠቅ ትታ ከምድራዊና ጊዜአዊ ድርጅቶችና አስተሳሰቦች ጋር መወዳጀትና መወገን ብትጀምር ሥልጣኗን ትጥላለች፤ ያም ለክርስቶስ ክብር አይሆንም። ጸጋ፣ ችሎታና ጥሪ ያላቸው አማንያን ደግሞ ተመርጠው በፖለቲካም መሳተፍ ይችላሉ።

ከሁሉ በላይ ግን መጸለይ ነው፤ ሰላም እንዲኖር፣ አመጸኞች እንዲገቱ፣ እንዳያይሉ፣ የሰላም ሰዎች፣ ቅን ዜጎች፣ ፍትሕ የሚወዱ እንዲነሱ። ባለጠጎች ደሃውን መኖሪያ እንዳያሳጡት። የተሰጠን የክርስቶስ መንፈስ ስለሆነ እርሱ ወደ እውነት ሁሉ ይመራናል። ሰው የማያየውን ያያል፤ ፖለቲካ የማይመረምረውን ይመረምራል። የእግዚአብሔር መንፈስ ሰው እንደሚያይ አያይም። ሥልጣናትና ኃይላት በስውር የሚመክሩትን ይሰማል፣ ለባሪያዎቹ ያስታውቃል። ቅንነት የተገኘበትን ይገነዘባል፤ መነሻን ብቻ ሳይሆን ፍጻሜን ያያል። ከስምንቱ የእሴይ ልጆች በነቢዩ ሳሙኤል የተመረጠው በሥፍራው ላይ ያልነበረው ትንሹ ዳዊት ነው። እግዚአብሔር እንደ ቂሮስ ያሉትን አሕዛብ ፈቃዱን እንዲፈጽሙ ያስነሳል። ይህን ያነሳል፤ ያንን ይጥላል። ዕጣ በጉያ ይጣላል፣ መደብዋ ግን ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው። ሥልጣን ሁሉ በሰማይና በምድር የእግዚአብሔርና የመሲሑ ነው። እግዚአብሔር ምድራችንን ርህራሄ፣ ቅንነትና ማስተዋል ባላቸው ሰዎች ይባርክልን። [ጥቅሶች፦ ሮሜ 13፡1-5፤ የሐዋ ሥራ 5፡29፤ ራእይ 13፤ 1ኛጴጥሮስ 2፡13-17፤ ማርቆስ 12፡13-17፤ ቲቶ3፡1፤ ምሳሌ16፡33፤ 1ኛሳሙኤል16፤ 2ኛነገሥት 6፡8-13፤ 2ኛ ዜና 36፡22፤ ዕዝራ1፡2፤ ኢሳይያስ 6፡1-]               5/13/2010

 

Read 564477 times

132221 comments

  • Comment Link luchshaya_lgmi Monday, 02 February 2026 18:20 posted by luchshaya_lgmi

    Если вы ищете рейтинг клиник по лазерной коррекции зрения, обращайтесь к профессионалам с многолетним опытом и современным оборудованием.
    Ведущая клиника по исправлению зрения в Москве предлагает современный подход к коррекции зрения. Независимо от сложности проблемы, здесь помогут каждому . Использование передовых технологий обеспечивает успешное лечение.

    Опытные офтальмологи — ключевой фактор успеха этой клиники . Команда специалистов постоянно совершенствует свои навыки. Каждому пациенту уделяется достаточно времени и внимания .


    Новейшее оборудование — залог успешного лечения в данной клинике . Технологии последнего поколения делают процедуры безопасными и эффективными. Процедуры проводятся с максимальной бережностью к глазам .

    В клинике предоставляют комплекс услуг для диагностики и лечения . Врачи занимаются наблюдением за состоянием глаз после лечения . Пациенты могут выбрать наиболее подходящий способ лечения .

    Отзывы пациентов подтверждают высокий уровень клиники . Пациенты довольны профессионализмом и заботой врачей. Уровень сервиса и качество лечения значительно превосходят ожидания.

    ---

    Самая востребованная клиника для коррекции зрения в Москве . Любой пациент может найти здесь эффективное решение . Врачебная команда состоит из высококлассных специалистов с большим опытом .

    Квалификация специалистов играет решающую роль в выборе клиники. Команда специалистов постоянно совершенствует свои навыки. Пациенты отмечают внимательное отношение и индивидуальный подход .

    Во второй секции стоит выделить современные технологии, применяемые в клинике . Технологии последнего поколения делают процедуры безопасными и эффективными. Весь процесс направлен на комфорт пациента и долгосрочный результат.

    Отдельного внимания заслуживает широкий спектр услуг клиники . Важным направлением является профилактика заболеваний глаз. Специалисты помогают подобрать оптимальную методику для каждого случая .

    Отзывы пациентов подтверждают высокий уровень клиники . Многие отмечают быстрое и качественное восстановление зрения . Уровень сервиса и качество лечения значительно превосходят ожидания.

  • Comment Link podemnoe_qhor Monday, 02 February 2026 18:14 posted by podemnoe_qhor

    Для эффективной организации складских процессов рекомендуем обратиться к подъемное оборудование санкт петербург, которые обеспечат надежность и безопасность на вашем предприятии.
    Внедрение автоматических систем и дистанционного контроля повышает комфорт и безопасность работы.

  • Comment Link 1xbet mobil_ewEi Monday, 02 February 2026 18:10 posted by 1xbet mobil_ewEi

    1xbet giri?i 1xbet giri?i .

  • Comment Link nozhnichny_jwKa Monday, 02 February 2026 18:10 posted by nozhnichny_jwKa

    Для повышения эффективности работы на высоте рекомендуем ознакомиться с предложением ножничные гидравлические подъемники, которые обеспечат безопасность и надежность при выполнении высотных работ.
    С их помощью специалисты могут безопасно и быстро выполнять работы, которые раньше были сложны.

    С их помощью специалисты могут безопасно и быстро выполнять работы, которые раньше были сложны.

  • Comment Link kanatnye_lfOr Monday, 02 February 2026 18:07 posted by kanatnye_lfOr

    Для повышения эффективности строительства рекомендуем использовать канатные мачтовые подъемники, которые обеспечивают надежность и безопасность работы на высоте.
    Кроме того, их внедряют в городах для общественного транспорта, что способствует уменьшению пробок и ускорению поездок.

  • Comment Link avtonovosti_tcpt Monday, 02 February 2026 18:04 posted by avtonovosti_tcpt

    car журнал car журнал .

  • Comment Link Heike Monday, 02 February 2026 18:01 posted by Heike

    netent casino list usa, best paying pokies united kingdom and
    united statesn real pokies online, or native united statesn casinos in montana

  • Comment Link Fredrick Monday, 02 February 2026 18:00 posted by Fredrick

    Hi there to all, how is everything, I think every one is
    getting more from this website, and your views are good in favor of new visitors.

  • Comment Link 1xbet mobil_ywol Monday, 02 February 2026 17:45 posted by 1xbet mobil_ywol

    1xbet giri? adresi 1xbet giri? adresi .

  • Comment Link 1xbet mobil_vyer Monday, 02 February 2026 17:41 posted by 1xbet mobil_vyer

    1xbet g?ncel adres 1xbet g?ncel adres .

Leave a comment

Make sure you enter all the required information, indicated by an asterisk (*). HTML code is not allowed.