×

Warning

JUser: :_load: Unable to load user with ID: 42
Sunday, 13 November 2011 21:04

ያለ ዕውቀት መቅናት Featured

Rate this item
(0 votes)

የሚከተለው ርዕሰ አንቀጽ፣ ማኅበረ በኵር ካሳተመው፣ ከጮራ መጽሔት ቁጥር 34፣ ገጽ 1-2 ላይ የተወሰደ ሲሆን፣ ለብዙዎች እንዲዳረስ በማሰብ ለጥፈነዋል። ይህን ጽሑፍ ያዘጋጁትን ወገኖች እግዚአብሔር ይባርካቸው።

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፣ አሜን።

ያለ ዕውቀት መቅናት

ቅንአትን ሥጋዊና መንፈሳዊ ብሎ ለሁለት ከፍሎ ማየት የተለመደ ሆኗል። ሥጋዊ ቅናት በጥቅሉ ሲታይ፣ በሌላው ሰው ማደግና አንዳች ነገር ማግኘት ደስ አለ መሰኘትና የሌላው ይሆን ዘንድ ያልወደዱትን ለራስ ለማድረግ መፈለግ በመሆኑ ፍቺው ብዙም አያደናግርም። በመንፈሳዊ ስም የሚጠራው ቅናት ግን ሁል ጊዜ መንፈሳዊ ነው ለማለት ይቸግራል። እንዲያውም መንፈሳዊ ካባ የደረበ ሥጋዊ ቅናት ሆኖ የሚገለጥበት አጋጣሚ ጥቂት አይደለም።

እንዲህ ያለውን መንፈስ ለበስ ሥጋዊ ቅናት ሐዋርያው ጳውሎስ፣ ‘ያለ ዕውቀት መቅናት’ ይለዋል። ይህን ያለውም የዘመዶቹን የአይሁድን ቅንአት ምንነት በገለጸበት ክፍል ነው። እነርሱ ለእግዚአብሔር የሚቀኑ መሆናቸውን ሐዋርያው አልሸሸገም፤ ለእግዚአብሔር የቀኑ ይሁኑ እንጂ፣ ቅንአታቸው በዕውቀት ላይ ስላልተመሠረተ የራሳቸውን ጽድቅ ለማቆም በመፈለግ ለእግዚአብሔር ጽድቅ መገዛትን እንቢ አሉ [ሮሜ 10፣13]።

እንዲህ ባለው ቀናተኛነት ውስጥ ጳውሎስ የተባለው ሳውልም ዐልፏል። ለሙሴ ሕግ በመቅናት እግዚአብሔርን ያገለገለ እየመሰለው የክርስቶስን ተከታዮች በጽኑ ያሳድድ ነበር። በክርስቶስ ወደ ማመን ከተመለሰ በኋላ፣ በትዝታ ወደ ኋላ ተመልሶ በአይሁድ መካከል የሰጠው ምስክርነት ይህንኑ ያስረዳል። “እኔ … የአባቶቼንም ሕግ ጠንቅቄ የተማርሁ፣ ዛሬውንም እናንተ ሁሉ እንድትሆኑ ለእግዚአብሔር ቀናተኛ የሆንሁ አይሁዳዊ ነኝ። ወንዶችንም ሴቶችንም እያሰርሁ ወደ ወኅኒም አሳልፌ እየሰጠሁ ይህን መንገድ [ክርስትናን] እስከ ሞት ድረስ አሳደድሁ” [የሐዋርያት ሥራ 22:3-4]። እንዲሁም ለፊልጵስዩስ ምእመናን በጻፈው መልእክቱ፣ “ስለ ቅንአት ብትጠይቁ፣ ቤተ ክርስቲያንን አሳዳጅ ነበርሁ፤” ብሏል [3:6]። ምናልባትም ይህ በዘመኑ አይሁድ ዘንድ የቀናተኛነት ጣሪያ ተደርጎ ሳይወሰድ አልቀረም። ምክንያቱም ጳውሎስ ‘በቅንአትም ቢሆን እኔን የሚበልጥ ማንም የለም’ እያለ ነውና የሚናገረው [ቁ.4]። ይህ ሁሉ ግን፣ የሙሴ ሕግ የተሰጠው ፍጹም የሆነው [ወንጌል] እስኪመጣ ድረስ መሆኑን ካለማወቅ የመጣ ዐጕል ቅናት እንደ ሆነ ለመገንዘብ አያስቸግርም። ያለ ዕውቀት መቅናት ይሏል ይህ ነው።

ጳውሎስ ይህንና የመሳሰለውን ኢመንፈሳዊ ድርጊት ክርስትና ላይ ቆሞ ሲያስታውሰው፣ እንደ መልካም ሥራ ሳይሆን “እንደ ጕድፍ”፣ “እንደ ጕዳት”ም ነው የቆጠረው [ቁ.7-9]። ምክንያቱም ጌታ በወንጌል፣ “እንዳትሰናከሉ ይህን ተናግሬአችኋለሁ። ከምኵራባቸው ያወጡአችኋል፤ ከምንም በላይ ደግሞ የሚገላችሁ ሁሉ እግዚአብሔርን እንደሚያገለግል የሚመስልበት ጊዜ ይመጣል” [ዮሐንስ 16:1-2] በማለቱ፣ እንዲህ ያለው ቅንአት፦ እግዚአብሔርን የሚያሳዝን እንጂ የማያስደስት ቅንአት፣ ከእግዚአብሔር ዘንድ ክብርና ምስጋናን የሚያሰጥ ሳይሆን በኀጢአተኛነት የሚያስጠይቅና ኵነኔን የሚያስከትል ቅንአት፣ እንዲያው በጥቅሉ ባዶ ቅንአት መሆኑን አስተውሏል።

ዛሬም እንደ አይሁድ ለእግዚአብሔር በመቅናት ስም ከእግዚአብሔር ፈቃድ ውጪ የሚመላለሱ ሞልተዋል። በዘመናችን ለእናት ቤተ ክርስቲያን ህልውና ቀንተው የተነሡ ብዙዎች፣ ቅንአታቸውና ለቤተ ክርስቲያናቸው ያላቸው ፍቅር በራሱ ደስ የሚያሰኝ ነው ሊባል ቢችልም፣ ቅንአታቸውን የሚያሳዩበት መንገድ ግን በአብዛኛው ክርስቲያናዊናመንፈሳዊ ሆኖ አይታይም፤ በዕውቀት ላይ ስላልተመሠረተም ከአይሁድ ቅንአት የተለየ አይደለም።

ቅንአታቸው በእግዚአብሔር ቃል ዕውቀት ላይ በተመሠረተ የእግዚአብሔር ፈቃድ የሚመራ አለ መሆኑ ዋናው መሠረታዊ ችግር ተደርጎ ይወሰዳል። ቤተ ክርስቲያንን እንደ አንድምድራዊት ድርጅት በመቍጠር፣ ህልውናዋን የእግዚአብሔርን ቃል በጥራት በማስተማር ሳይሆን በምድራዊ ጥበብና በሥጋዊ ኀይል ለማስጠበቅ ላይ ታች ይላሉ። የቤተ ክርስቲያን ዐውደ ምሕረት በወንጌሉ ቃል ሳይሆን ማለቂያ በሌለው፣ የአሮጊቶችን ተረት በመሰለ ትምህርት እንዲሞላ ለማድረግ ይታገላሉ። ቤተ ክርስቲያን በቃለ እግዚአብሔር ወልዳ ያሳደገቻቸውንና ደረሱልኝ ብላ ተስፋ የጣለችባቸውን አገልጋዮቿን፣ ብርሃኑን ጨለማ፣ ጨለማውን ብርሃን፣ መልካሙን ክፉ፣ ክፉውን መልካም፣ ጣፋጩን መራራ፣ መራራውን ጣፋጭ [ኢሳይያስ 5:20] በማለት የተለያየ ስም እያወጡ ያሳድዳሉ። በሌሎች አስታከው ወንጌልንና የወንጌል እንብርት የሆነውን ኢየሱስን ይቃወማሉ። ውስጣዊ ዐይኖቻቸው በርተው እነዚህንና ሌሎችንም ክፉ ሥራዎቻቸውን፣ ለእግዚአብሔር በእውነት ቀንተው ስሙን ካስከበሩት እውነተኛ አገልጋዮቹ ሥራ ጋር ቢያስተያዩት ምንኛ ባፈሩ! ድርጊታቸውንም እንደ ጳውሎስ ጕዳትና ጕድፍ አድርገው በቆጠሩት ነበር።

ከመንፈሳዊ ቅንአት አንጻር፣ ከላይ ከተዘረዘሩት ክፉ ሥራዎች መካከል አንዱ ስንኳ ለእግዚአብሔር መቅናትን ማሳያ ሆኖ ሊጠቀስ አይችልም። ቤተ ክርስቲያን የገሃነም ደጆች የማይችሏት ሆኖ በክርስቶስ የተመሠረተች የእግዚአብሔር መንግሥት እንጂ፣ በሰዎች ስምምነት የተቋቋመች ምድራዊ ድርጅት ወይም “ኀላፊነቱ የተወሰነ የኅብረት ሥራ ማኅበር” አይደለችምና ጠባቂዋ ራሱ ጌታ እግዚአብሔር መሆኑ በቅድሚያ መታወቅ አለበት። የሥልጣኗና የትምህርቷ መሠረት፣ የህልውናዋ መጠበቂያም ሌሎች የፈጠራ ጽሑፎች ሳይሆኑ መጽሐፍ ቅዱስ ነው። ቤተ ክርስቲያን በወንጌል ምክንያት መሰደድ እንጂ ማሳደድ ከክርስቶስና ከሐዋርያቱ የተማረችው፣ የተቀበለችውም ግብሯ አይደለም። የወንጌልን ማእከላዊ መልእክት ክርስቶስን በመስበክ የምሥራቹን ቃል ታበሥራለች እንጂ፣ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ መንገድ ክርስቶስንና ወንጌሉን አትቃወምም።

አይሁድ ለሙሴ ሕግ ቀንተው ክርስቶስን በመስቀላቸው፣ ተከታዮቹ ሐዋርያትንም ተቃውመው እስከ ሞት ድረስ በማሳደዳቸው እግዚአብሔርን አሳዘኑት እንጂ ደስ አላሰኙትም። “እነርሱ ጌታ ኢየሱስንና ነቢያትን ገደሉ፤ እኛንም አሳደዱን፣ እግዚአብሔርንም ደስ አላሰኙትም፤ የሰውም ሁሉ ፀር ሆኑ፤ ይኸውም ይድኑ ዘንድ ለአሕዛብ እንዳንናገር ለመከልከል ነው፤ በዚህ ሁኔታ ኀጢአታቸውን ሁል ጊዜ በራሳቸው ላይ እስከ መጨረሻው እያከማቹ ይሄዳሉ። ቁጣውም በእነርሱ ላይ ያለ ልክ መጥቶአል” [1ኛ ተሰሎንቄ 2:15-16፤ ዐ.መ.ት.]። ስለዚህ በአይሁድ መንገድ ቀናተኛ የሆኑ ሁሉ፣ እንደ ጳውሎስ ጌታንና ቤተ ክርስቲያንን ከማሳደድ ተመልሰው ስለ ጌታ ስም ለመሰደድ ራሳቸውን ካላዘጋጁ፣ ስለ ገፉት የእግዚአብሔር ጽድቅና ስለ ፈጸሙት ኀጢአት፣ በዚህ ዓለም በተለያየ መከራና ችግር ይቀጣሉ፤ በመጨረሻው ቀንም ይጠየቁበታል።

ሰላም ሊሰጣት የመጣውን ጌታን በመቃወም ሰቅላ ለገደለችው፣ ወደ እርስዋም የተላኩ ነቢያትን ላሳደደችው ለኢየሩሳሌም በራሱ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ፣ “ኢየሩሳሌም፣ ኢየሩሳሌም ነቢያትን የምትገድል፣ ዶሮ ጫጩቶችዋን ከክንፉችዋ በታች እንደምትሰበስብ ልጆችሽን እሰበስብ ዘንድ ስንት ጊዜ ወደድሁ! [እናንተ ግን] አልወደዳችሁምም። እነሆ ቤታችሁ የተፈታ ሆኖ ይቀርላችኋል” [ማቴዎስ 23:37-38] ተብሎ እንደ ተነገረባት፣ በ 70 ዓ.ም. ሮማውያን አወደሟት፤ ብዙ አይሁድም ዐለቁ።

ዛሬም ያለ ዕውቀት “ቀናተኛ” የሆኑ ሁሉ፣ ኢየሩሳሌም ለእግዚአብሔር በመቅናት ስም ከፈጸመችው ዐመፅና ዐመፅዋ ካስከተለባት ከዚህ ጥፋት መማር አለባቸው። ለእግዚአብሔር ቀንተናል በሚል እግዚአብሔርን ሲቃወሙ እንዳይገኙ ሊጠነቀቁ ይገባል። ለሰላማቸው የሚሆነውን የክርስቶስን ወንጌል መቃወማቸውንና የእግዚአብሔርን ቃል የሚያስተምሯቸውን ማሳደዳቸውን የሚገፉበት ከሆነ ግን፣ የዘላለም ሕይወት እንዳይገባቸው በራሳቸው ላይ ፈርደዋል ማለት ነው [የሐዋርያት ሥራ 13:46]።

Read 620408 times

127152 comments

  • Comment Link Robertfus Sunday, 29 March 2026 05:24 posted by Robertfus

    BlackSprut marketplace официальный сайт для входа и регистрации
    blsp at bs2best at

    bs2best вход

  • Comment Link kyhni SPb_ctMa Sunday, 29 March 2026 05:07 posted by kyhni SPb_ctMa

    кухни от производителя спб недорого и качественно kuhni-spb-49.ru .

  • Comment Link hot646 Sunday, 29 March 2026 05:03 posted by hot646

    Hello there! Would you mind if I share your blog with my facebook group? There's a lot of people that I think would really enjoy your content. Please let me know. Thank you

  • Comment Link zakazat kyhnu_hgEa Sunday, 29 March 2026 05:01 posted by zakazat kyhnu_hgEa

    заказать индивидуальную кухню zakazat-kuhnyu-9.ru .

  • Comment Link zakazat kyhnu_zsor Sunday, 29 March 2026 05:01 posted by zakazat kyhnu_zsor

    заказать кухню в рассрочку zakazat-kuhnyu-12.ru .

  • Comment Link zakazat kyhnu_qpPa Sunday, 29 March 2026 04:58 posted by zakazat kyhnu_qpPa

    заказать кухню на заказ заказать кухню на заказ .

  • Comment Link Narkolog na dom v Krasnodare_sgmt Sunday, 29 March 2026 04:15 posted by Narkolog na dom v Krasnodare_sgmt

    вызвать нарколога на дом вызвать нарколога на дом .

  • Comment Link reklamnii kreativ_rbPt Sunday, 29 March 2026 03:55 posted by reklamnii kreativ_rbPt

    анализ карточек маркетплейс анализ карточек маркетплейс .

  • Comment Link Betsson Sunday, 29 March 2026 03:54 posted by Betsson

    https://betsson.net.co/
    A Betsson nao e uma operadora qualquer; com uma historia que ultrapassa seis decadas desde sua fundacao no ano de 1963, na Suecia, estabeleceu um nome forte nos mercados regulados, como e o caso da Colombia sob a regulamentacao da Coljuegos.

  • Comment Link Betsson Sunday, 29 March 2026 03:54 posted by Betsson

    https://betsson.net.co/
    A Betsson esta longe de ser um operador comum; com mais de sessenta anos de experiencia desde que foi fundada na Suecia, em 1963, consagrou sua credibilidade no mercado regulado, com presenca tambem na Colombia sob a regulamentacao da Coljuegos.

Leave a comment

Make sure you enter all the required information, indicated by an asterisk (*). HTML code is not allowed.