×

Warning

JUser: :_load: Unable to load user with ID: 42
Sunday, 13 November 2011 21:04

ያለ ዕውቀት መቅናት Featured

Rate this item
(0 votes)

የሚከተለው ርዕሰ አንቀጽ፣ ማኅበረ በኵር ካሳተመው፣ ከጮራ መጽሔት ቁጥር 34፣ ገጽ 1-2 ላይ የተወሰደ ሲሆን፣ ለብዙዎች እንዲዳረስ በማሰብ ለጥፈነዋል። ይህን ጽሑፍ ያዘጋጁትን ወገኖች እግዚአብሔር ይባርካቸው።

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፣ አሜን።

ያለ ዕውቀት መቅናት

ቅንአትን ሥጋዊና መንፈሳዊ ብሎ ለሁለት ከፍሎ ማየት የተለመደ ሆኗል። ሥጋዊ ቅናት በጥቅሉ ሲታይ፣ በሌላው ሰው ማደግና አንዳች ነገር ማግኘት ደስ አለ መሰኘትና የሌላው ይሆን ዘንድ ያልወደዱትን ለራስ ለማድረግ መፈለግ በመሆኑ ፍቺው ብዙም አያደናግርም። በመንፈሳዊ ስም የሚጠራው ቅናት ግን ሁል ጊዜ መንፈሳዊ ነው ለማለት ይቸግራል። እንዲያውም መንፈሳዊ ካባ የደረበ ሥጋዊ ቅናት ሆኖ የሚገለጥበት አጋጣሚ ጥቂት አይደለም።

እንዲህ ያለውን መንፈስ ለበስ ሥጋዊ ቅናት ሐዋርያው ጳውሎስ፣ ‘ያለ ዕውቀት መቅናት’ ይለዋል። ይህን ያለውም የዘመዶቹን የአይሁድን ቅንአት ምንነት በገለጸበት ክፍል ነው። እነርሱ ለእግዚአብሔር የሚቀኑ መሆናቸውን ሐዋርያው አልሸሸገም፤ ለእግዚአብሔር የቀኑ ይሁኑ እንጂ፣ ቅንአታቸው በዕውቀት ላይ ስላልተመሠረተ የራሳቸውን ጽድቅ ለማቆም በመፈለግ ለእግዚአብሔር ጽድቅ መገዛትን እንቢ አሉ [ሮሜ 10፣13]።

እንዲህ ባለው ቀናተኛነት ውስጥ ጳውሎስ የተባለው ሳውልም ዐልፏል። ለሙሴ ሕግ በመቅናት እግዚአብሔርን ያገለገለ እየመሰለው የክርስቶስን ተከታዮች በጽኑ ያሳድድ ነበር። በክርስቶስ ወደ ማመን ከተመለሰ በኋላ፣ በትዝታ ወደ ኋላ ተመልሶ በአይሁድ መካከል የሰጠው ምስክርነት ይህንኑ ያስረዳል። “እኔ … የአባቶቼንም ሕግ ጠንቅቄ የተማርሁ፣ ዛሬውንም እናንተ ሁሉ እንድትሆኑ ለእግዚአብሔር ቀናተኛ የሆንሁ አይሁዳዊ ነኝ። ወንዶችንም ሴቶችንም እያሰርሁ ወደ ወኅኒም አሳልፌ እየሰጠሁ ይህን መንገድ [ክርስትናን] እስከ ሞት ድረስ አሳደድሁ” [የሐዋርያት ሥራ 22:3-4]። እንዲሁም ለፊልጵስዩስ ምእመናን በጻፈው መልእክቱ፣ “ስለ ቅንአት ብትጠይቁ፣ ቤተ ክርስቲያንን አሳዳጅ ነበርሁ፤” ብሏል [3:6]። ምናልባትም ይህ በዘመኑ አይሁድ ዘንድ የቀናተኛነት ጣሪያ ተደርጎ ሳይወሰድ አልቀረም። ምክንያቱም ጳውሎስ ‘በቅንአትም ቢሆን እኔን የሚበልጥ ማንም የለም’ እያለ ነውና የሚናገረው [ቁ.4]። ይህ ሁሉ ግን፣ የሙሴ ሕግ የተሰጠው ፍጹም የሆነው [ወንጌል] እስኪመጣ ድረስ መሆኑን ካለማወቅ የመጣ ዐጕል ቅናት እንደ ሆነ ለመገንዘብ አያስቸግርም። ያለ ዕውቀት መቅናት ይሏል ይህ ነው።

ጳውሎስ ይህንና የመሳሰለውን ኢመንፈሳዊ ድርጊት ክርስትና ላይ ቆሞ ሲያስታውሰው፣ እንደ መልካም ሥራ ሳይሆን “እንደ ጕድፍ”፣ “እንደ ጕዳት”ም ነው የቆጠረው [ቁ.7-9]። ምክንያቱም ጌታ በወንጌል፣ “እንዳትሰናከሉ ይህን ተናግሬአችኋለሁ። ከምኵራባቸው ያወጡአችኋል፤ ከምንም በላይ ደግሞ የሚገላችሁ ሁሉ እግዚአብሔርን እንደሚያገለግል የሚመስልበት ጊዜ ይመጣል” [ዮሐንስ 16:1-2] በማለቱ፣ እንዲህ ያለው ቅንአት፦ እግዚአብሔርን የሚያሳዝን እንጂ የማያስደስት ቅንአት፣ ከእግዚአብሔር ዘንድ ክብርና ምስጋናን የሚያሰጥ ሳይሆን በኀጢአተኛነት የሚያስጠይቅና ኵነኔን የሚያስከትል ቅንአት፣ እንዲያው በጥቅሉ ባዶ ቅንአት መሆኑን አስተውሏል።

ዛሬም እንደ አይሁድ ለእግዚአብሔር በመቅናት ስም ከእግዚአብሔር ፈቃድ ውጪ የሚመላለሱ ሞልተዋል። በዘመናችን ለእናት ቤተ ክርስቲያን ህልውና ቀንተው የተነሡ ብዙዎች፣ ቅንአታቸውና ለቤተ ክርስቲያናቸው ያላቸው ፍቅር በራሱ ደስ የሚያሰኝ ነው ሊባል ቢችልም፣ ቅንአታቸውን የሚያሳዩበት መንገድ ግን በአብዛኛው ክርስቲያናዊናመንፈሳዊ ሆኖ አይታይም፤ በዕውቀት ላይ ስላልተመሠረተም ከአይሁድ ቅንአት የተለየ አይደለም።

ቅንአታቸው በእግዚአብሔር ቃል ዕውቀት ላይ በተመሠረተ የእግዚአብሔር ፈቃድ የሚመራ አለ መሆኑ ዋናው መሠረታዊ ችግር ተደርጎ ይወሰዳል። ቤተ ክርስቲያንን እንደ አንድምድራዊት ድርጅት በመቍጠር፣ ህልውናዋን የእግዚአብሔርን ቃል በጥራት በማስተማር ሳይሆን በምድራዊ ጥበብና በሥጋዊ ኀይል ለማስጠበቅ ላይ ታች ይላሉ። የቤተ ክርስቲያን ዐውደ ምሕረት በወንጌሉ ቃል ሳይሆን ማለቂያ በሌለው፣ የአሮጊቶችን ተረት በመሰለ ትምህርት እንዲሞላ ለማድረግ ይታገላሉ። ቤተ ክርስቲያን በቃለ እግዚአብሔር ወልዳ ያሳደገቻቸውንና ደረሱልኝ ብላ ተስፋ የጣለችባቸውን አገልጋዮቿን፣ ብርሃኑን ጨለማ፣ ጨለማውን ብርሃን፣ መልካሙን ክፉ፣ ክፉውን መልካም፣ ጣፋጩን መራራ፣ መራራውን ጣፋጭ [ኢሳይያስ 5:20] በማለት የተለያየ ስም እያወጡ ያሳድዳሉ። በሌሎች አስታከው ወንጌልንና የወንጌል እንብርት የሆነውን ኢየሱስን ይቃወማሉ። ውስጣዊ ዐይኖቻቸው በርተው እነዚህንና ሌሎችንም ክፉ ሥራዎቻቸውን፣ ለእግዚአብሔር በእውነት ቀንተው ስሙን ካስከበሩት እውነተኛ አገልጋዮቹ ሥራ ጋር ቢያስተያዩት ምንኛ ባፈሩ! ድርጊታቸውንም እንደ ጳውሎስ ጕዳትና ጕድፍ አድርገው በቆጠሩት ነበር።

ከመንፈሳዊ ቅንአት አንጻር፣ ከላይ ከተዘረዘሩት ክፉ ሥራዎች መካከል አንዱ ስንኳ ለእግዚአብሔር መቅናትን ማሳያ ሆኖ ሊጠቀስ አይችልም። ቤተ ክርስቲያን የገሃነም ደጆች የማይችሏት ሆኖ በክርስቶስ የተመሠረተች የእግዚአብሔር መንግሥት እንጂ፣ በሰዎች ስምምነት የተቋቋመች ምድራዊ ድርጅት ወይም “ኀላፊነቱ የተወሰነ የኅብረት ሥራ ማኅበር” አይደለችምና ጠባቂዋ ራሱ ጌታ እግዚአብሔር መሆኑ በቅድሚያ መታወቅ አለበት። የሥልጣኗና የትምህርቷ መሠረት፣ የህልውናዋ መጠበቂያም ሌሎች የፈጠራ ጽሑፎች ሳይሆኑ መጽሐፍ ቅዱስ ነው። ቤተ ክርስቲያን በወንጌል ምክንያት መሰደድ እንጂ ማሳደድ ከክርስቶስና ከሐዋርያቱ የተማረችው፣ የተቀበለችውም ግብሯ አይደለም። የወንጌልን ማእከላዊ መልእክት ክርስቶስን በመስበክ የምሥራቹን ቃል ታበሥራለች እንጂ፣ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ መንገድ ክርስቶስንና ወንጌሉን አትቃወምም።

አይሁድ ለሙሴ ሕግ ቀንተው ክርስቶስን በመስቀላቸው፣ ተከታዮቹ ሐዋርያትንም ተቃውመው እስከ ሞት ድረስ በማሳደዳቸው እግዚአብሔርን አሳዘኑት እንጂ ደስ አላሰኙትም። “እነርሱ ጌታ ኢየሱስንና ነቢያትን ገደሉ፤ እኛንም አሳደዱን፣ እግዚአብሔርንም ደስ አላሰኙትም፤ የሰውም ሁሉ ፀር ሆኑ፤ ይኸውም ይድኑ ዘንድ ለአሕዛብ እንዳንናገር ለመከልከል ነው፤ በዚህ ሁኔታ ኀጢአታቸውን ሁል ጊዜ በራሳቸው ላይ እስከ መጨረሻው እያከማቹ ይሄዳሉ። ቁጣውም በእነርሱ ላይ ያለ ልክ መጥቶአል” [1ኛ ተሰሎንቄ 2:15-16፤ ዐ.መ.ት.]። ስለዚህ በአይሁድ መንገድ ቀናተኛ የሆኑ ሁሉ፣ እንደ ጳውሎስ ጌታንና ቤተ ክርስቲያንን ከማሳደድ ተመልሰው ስለ ጌታ ስም ለመሰደድ ራሳቸውን ካላዘጋጁ፣ ስለ ገፉት የእግዚአብሔር ጽድቅና ስለ ፈጸሙት ኀጢአት፣ በዚህ ዓለም በተለያየ መከራና ችግር ይቀጣሉ፤ በመጨረሻው ቀንም ይጠየቁበታል።

ሰላም ሊሰጣት የመጣውን ጌታን በመቃወም ሰቅላ ለገደለችው፣ ወደ እርስዋም የተላኩ ነቢያትን ላሳደደችው ለኢየሩሳሌም በራሱ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ፣ “ኢየሩሳሌም፣ ኢየሩሳሌም ነቢያትን የምትገድል፣ ዶሮ ጫጩቶችዋን ከክንፉችዋ በታች እንደምትሰበስብ ልጆችሽን እሰበስብ ዘንድ ስንት ጊዜ ወደድሁ! [እናንተ ግን] አልወደዳችሁምም። እነሆ ቤታችሁ የተፈታ ሆኖ ይቀርላችኋል” [ማቴዎስ 23:37-38] ተብሎ እንደ ተነገረባት፣ በ 70 ዓ.ም. ሮማውያን አወደሟት፤ ብዙ አይሁድም ዐለቁ።

ዛሬም ያለ ዕውቀት “ቀናተኛ” የሆኑ ሁሉ፣ ኢየሩሳሌም ለእግዚአብሔር በመቅናት ስም ከፈጸመችው ዐመፅና ዐመፅዋ ካስከተለባት ከዚህ ጥፋት መማር አለባቸው። ለእግዚአብሔር ቀንተናል በሚል እግዚአብሔርን ሲቃወሙ እንዳይገኙ ሊጠነቀቁ ይገባል። ለሰላማቸው የሚሆነውን የክርስቶስን ወንጌል መቃወማቸውንና የእግዚአብሔርን ቃል የሚያስተምሯቸውን ማሳደዳቸውን የሚገፉበት ከሆነ ግን፣ የዘላለም ሕይወት እንዳይገባቸው በራሳቸው ላይ ፈርደዋል ማለት ነው [የሐዋርያት ሥራ 13:46]።

Read 543340 times

105387 comments

  • Comment Link Fonda Peevey Wednesday, 17 December 2025 21:24 posted by Fonda Peevey

    Today, while I was at work, my sister stole my iPad and tested to see if it can survive a twenty five foot drop, just so she can be a youtube sensation. My iPad is now broken and she has 83 views. I know this is entirely off topic but I had to share it with someone!

  • Comment Link learn the facts here now Wednesday, 17 December 2025 21:23 posted by learn the facts here now

    obviously like your website however you have to take a look at the spelling on several of your posts.
    Many of them are rife with spelling problems and I to find
    it very troublesome to inform the truth nevertheless I will certainly come again again.

  • Comment Link corporate gift Wednesday, 17 December 2025 21:22 posted by corporate gift

    Hello there, I do think your blog could possibly be having internet
    browser compatibility problems. When I take a look at your site in Safari, it looks fine however, if
    opening in Internet Explorer, it's got some overlapping issues.
    I simply wanted to provide you with a quick heads up!

    Besides that, fantastic blog!

  • Comment Link nmghyuf Wednesday, 17 December 2025 21:09 posted by nmghyuf

    https://telegra.ph/Princip-dominanty-v-psihologii-Kak-soglasno-tipologii-eh-krechmera-nazyvaetsya-tip-stroeniya-tela-cheloveka-na-risunke-nizhe-Kak-12-17-3

  • Comment Link check this link right here now Wednesday, 17 December 2025 21:04 posted by check this link right here now

    We stumbled over here different web address
    and thought I may as well check things out. I like what I see so now i am following you.

    Look forward to looking at your web page for a second
    time.

  • Comment Link xmbaoyz Wednesday, 17 December 2025 20:50 posted by xmbaoyz

    https://telegra.ph/Princip-dominanty-v-psihologii-Kak-soglasno-tipologii-eh-krechmera-nazyvaetsya-tip-stroeniya-tela-cheloveka-na-risunke-nizhe-Kak-12-17-3

  • Comment Link look at here Wednesday, 17 December 2025 20:49 posted by look at here

    Hi outstanding website! Does running a blog similar to this require
    a lot of work? I have very little knowledge of coding however I was hoping to start my own blog in the near
    future. Anyway, should you have any recommendations or tips for new blog owners please share.
    I understand this is off topic but I just had to ask.

    Thank you!

  • Comment Link click for info Wednesday, 17 December 2025 20:45 posted by click for info

    Good day! This is kind of off topic but I need some advice from an established blog.
    Is it tough to set up your own blog? I'm not very techincal but I can figure things out pretty quick.
    I'm thinking about creating my own but I'm not sure where to begin.
    Do you have any ideas or suggestions? Appreciate it

  • Comment Link see here Wednesday, 17 December 2025 20:45 posted by see here

    This design is incredible! You definitely know how to keep a
    reader entertained. Between your wit and your videos, I was almost moved to start my own blog (well,
    almost...HaHa!) Great job. I really loved what you had to say,
    and more than that, how you presented it. Too cool!

  • Comment Link top video production company in delhi ncr Wednesday, 17 December 2025 20:44 posted by top video production company in delhi ncr

    Attractive component of content. I simply stumbled
    upon your blog and in accession capital to say that I get in fact loved account your blog posts.
    Anyway I will be subscribing in your feeds or even I success you access
    constantly rapidly.

Leave a comment

Make sure you enter all the required information, indicated by an asterisk (*). HTML code is not allowed.