×

Warning

JUser: :_load: Unable to load user with ID: 42
Sunday, 13 November 2011 21:04

ያለ ዕውቀት መቅናት Featured

Rate this item
(0 votes)

የሚከተለው ርዕሰ አንቀጽ፣ ማኅበረ በኵር ካሳተመው፣ ከጮራ መጽሔት ቁጥር 34፣ ገጽ 1-2 ላይ የተወሰደ ሲሆን፣ ለብዙዎች እንዲዳረስ በማሰብ ለጥፈነዋል። ይህን ጽሑፍ ያዘጋጁትን ወገኖች እግዚአብሔር ይባርካቸው።

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፣ አሜን።

ያለ ዕውቀት መቅናት

ቅንአትን ሥጋዊና መንፈሳዊ ብሎ ለሁለት ከፍሎ ማየት የተለመደ ሆኗል። ሥጋዊ ቅናት በጥቅሉ ሲታይ፣ በሌላው ሰው ማደግና አንዳች ነገር ማግኘት ደስ አለ መሰኘትና የሌላው ይሆን ዘንድ ያልወደዱትን ለራስ ለማድረግ መፈለግ በመሆኑ ፍቺው ብዙም አያደናግርም። በመንፈሳዊ ስም የሚጠራው ቅናት ግን ሁል ጊዜ መንፈሳዊ ነው ለማለት ይቸግራል። እንዲያውም መንፈሳዊ ካባ የደረበ ሥጋዊ ቅናት ሆኖ የሚገለጥበት አጋጣሚ ጥቂት አይደለም።

እንዲህ ያለውን መንፈስ ለበስ ሥጋዊ ቅናት ሐዋርያው ጳውሎስ፣ ‘ያለ ዕውቀት መቅናት’ ይለዋል። ይህን ያለውም የዘመዶቹን የአይሁድን ቅንአት ምንነት በገለጸበት ክፍል ነው። እነርሱ ለእግዚአብሔር የሚቀኑ መሆናቸውን ሐዋርያው አልሸሸገም፤ ለእግዚአብሔር የቀኑ ይሁኑ እንጂ፣ ቅንአታቸው በዕውቀት ላይ ስላልተመሠረተ የራሳቸውን ጽድቅ ለማቆም በመፈለግ ለእግዚአብሔር ጽድቅ መገዛትን እንቢ አሉ [ሮሜ 10፣13]።

እንዲህ ባለው ቀናተኛነት ውስጥ ጳውሎስ የተባለው ሳውልም ዐልፏል። ለሙሴ ሕግ በመቅናት እግዚአብሔርን ያገለገለ እየመሰለው የክርስቶስን ተከታዮች በጽኑ ያሳድድ ነበር። በክርስቶስ ወደ ማመን ከተመለሰ በኋላ፣ በትዝታ ወደ ኋላ ተመልሶ በአይሁድ መካከል የሰጠው ምስክርነት ይህንኑ ያስረዳል። “እኔ … የአባቶቼንም ሕግ ጠንቅቄ የተማርሁ፣ ዛሬውንም እናንተ ሁሉ እንድትሆኑ ለእግዚአብሔር ቀናተኛ የሆንሁ አይሁዳዊ ነኝ። ወንዶችንም ሴቶችንም እያሰርሁ ወደ ወኅኒም አሳልፌ እየሰጠሁ ይህን መንገድ [ክርስትናን] እስከ ሞት ድረስ አሳደድሁ” [የሐዋርያት ሥራ 22:3-4]። እንዲሁም ለፊልጵስዩስ ምእመናን በጻፈው መልእክቱ፣ “ስለ ቅንአት ብትጠይቁ፣ ቤተ ክርስቲያንን አሳዳጅ ነበርሁ፤” ብሏል [3:6]። ምናልባትም ይህ በዘመኑ አይሁድ ዘንድ የቀናተኛነት ጣሪያ ተደርጎ ሳይወሰድ አልቀረም። ምክንያቱም ጳውሎስ ‘በቅንአትም ቢሆን እኔን የሚበልጥ ማንም የለም’ እያለ ነውና የሚናገረው [ቁ.4]። ይህ ሁሉ ግን፣ የሙሴ ሕግ የተሰጠው ፍጹም የሆነው [ወንጌል] እስኪመጣ ድረስ መሆኑን ካለማወቅ የመጣ ዐጕል ቅናት እንደ ሆነ ለመገንዘብ አያስቸግርም። ያለ ዕውቀት መቅናት ይሏል ይህ ነው።

ጳውሎስ ይህንና የመሳሰለውን ኢመንፈሳዊ ድርጊት ክርስትና ላይ ቆሞ ሲያስታውሰው፣ እንደ መልካም ሥራ ሳይሆን “እንደ ጕድፍ”፣ “እንደ ጕዳት”ም ነው የቆጠረው [ቁ.7-9]። ምክንያቱም ጌታ በወንጌል፣ “እንዳትሰናከሉ ይህን ተናግሬአችኋለሁ። ከምኵራባቸው ያወጡአችኋል፤ ከምንም በላይ ደግሞ የሚገላችሁ ሁሉ እግዚአብሔርን እንደሚያገለግል የሚመስልበት ጊዜ ይመጣል” [ዮሐንስ 16:1-2] በማለቱ፣ እንዲህ ያለው ቅንአት፦ እግዚአብሔርን የሚያሳዝን እንጂ የማያስደስት ቅንአት፣ ከእግዚአብሔር ዘንድ ክብርና ምስጋናን የሚያሰጥ ሳይሆን በኀጢአተኛነት የሚያስጠይቅና ኵነኔን የሚያስከትል ቅንአት፣ እንዲያው በጥቅሉ ባዶ ቅንአት መሆኑን አስተውሏል።

ዛሬም እንደ አይሁድ ለእግዚአብሔር በመቅናት ስም ከእግዚአብሔር ፈቃድ ውጪ የሚመላለሱ ሞልተዋል። በዘመናችን ለእናት ቤተ ክርስቲያን ህልውና ቀንተው የተነሡ ብዙዎች፣ ቅንአታቸውና ለቤተ ክርስቲያናቸው ያላቸው ፍቅር በራሱ ደስ የሚያሰኝ ነው ሊባል ቢችልም፣ ቅንአታቸውን የሚያሳዩበት መንገድ ግን በአብዛኛው ክርስቲያናዊናመንፈሳዊ ሆኖ አይታይም፤ በዕውቀት ላይ ስላልተመሠረተም ከአይሁድ ቅንአት የተለየ አይደለም።

ቅንአታቸው በእግዚአብሔር ቃል ዕውቀት ላይ በተመሠረተ የእግዚአብሔር ፈቃድ የሚመራ አለ መሆኑ ዋናው መሠረታዊ ችግር ተደርጎ ይወሰዳል። ቤተ ክርስቲያንን እንደ አንድምድራዊት ድርጅት በመቍጠር፣ ህልውናዋን የእግዚአብሔርን ቃል በጥራት በማስተማር ሳይሆን በምድራዊ ጥበብና በሥጋዊ ኀይል ለማስጠበቅ ላይ ታች ይላሉ። የቤተ ክርስቲያን ዐውደ ምሕረት በወንጌሉ ቃል ሳይሆን ማለቂያ በሌለው፣ የአሮጊቶችን ተረት በመሰለ ትምህርት እንዲሞላ ለማድረግ ይታገላሉ። ቤተ ክርስቲያን በቃለ እግዚአብሔር ወልዳ ያሳደገቻቸውንና ደረሱልኝ ብላ ተስፋ የጣለችባቸውን አገልጋዮቿን፣ ብርሃኑን ጨለማ፣ ጨለማውን ብርሃን፣ መልካሙን ክፉ፣ ክፉውን መልካም፣ ጣፋጩን መራራ፣ መራራውን ጣፋጭ [ኢሳይያስ 5:20] በማለት የተለያየ ስም እያወጡ ያሳድዳሉ። በሌሎች አስታከው ወንጌልንና የወንጌል እንብርት የሆነውን ኢየሱስን ይቃወማሉ። ውስጣዊ ዐይኖቻቸው በርተው እነዚህንና ሌሎችንም ክፉ ሥራዎቻቸውን፣ ለእግዚአብሔር በእውነት ቀንተው ስሙን ካስከበሩት እውነተኛ አገልጋዮቹ ሥራ ጋር ቢያስተያዩት ምንኛ ባፈሩ! ድርጊታቸውንም እንደ ጳውሎስ ጕዳትና ጕድፍ አድርገው በቆጠሩት ነበር።

ከመንፈሳዊ ቅንአት አንጻር፣ ከላይ ከተዘረዘሩት ክፉ ሥራዎች መካከል አንዱ ስንኳ ለእግዚአብሔር መቅናትን ማሳያ ሆኖ ሊጠቀስ አይችልም። ቤተ ክርስቲያን የገሃነም ደጆች የማይችሏት ሆኖ በክርስቶስ የተመሠረተች የእግዚአብሔር መንግሥት እንጂ፣ በሰዎች ስምምነት የተቋቋመች ምድራዊ ድርጅት ወይም “ኀላፊነቱ የተወሰነ የኅብረት ሥራ ማኅበር” አይደለችምና ጠባቂዋ ራሱ ጌታ እግዚአብሔር መሆኑ በቅድሚያ መታወቅ አለበት። የሥልጣኗና የትምህርቷ መሠረት፣ የህልውናዋ መጠበቂያም ሌሎች የፈጠራ ጽሑፎች ሳይሆኑ መጽሐፍ ቅዱስ ነው። ቤተ ክርስቲያን በወንጌል ምክንያት መሰደድ እንጂ ማሳደድ ከክርስቶስና ከሐዋርያቱ የተማረችው፣ የተቀበለችውም ግብሯ አይደለም። የወንጌልን ማእከላዊ መልእክት ክርስቶስን በመስበክ የምሥራቹን ቃል ታበሥራለች እንጂ፣ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ መንገድ ክርስቶስንና ወንጌሉን አትቃወምም።

አይሁድ ለሙሴ ሕግ ቀንተው ክርስቶስን በመስቀላቸው፣ ተከታዮቹ ሐዋርያትንም ተቃውመው እስከ ሞት ድረስ በማሳደዳቸው እግዚአብሔርን አሳዘኑት እንጂ ደስ አላሰኙትም። “እነርሱ ጌታ ኢየሱስንና ነቢያትን ገደሉ፤ እኛንም አሳደዱን፣ እግዚአብሔርንም ደስ አላሰኙትም፤ የሰውም ሁሉ ፀር ሆኑ፤ ይኸውም ይድኑ ዘንድ ለአሕዛብ እንዳንናገር ለመከልከል ነው፤ በዚህ ሁኔታ ኀጢአታቸውን ሁል ጊዜ በራሳቸው ላይ እስከ መጨረሻው እያከማቹ ይሄዳሉ። ቁጣውም በእነርሱ ላይ ያለ ልክ መጥቶአል” [1ኛ ተሰሎንቄ 2:15-16፤ ዐ.መ.ት.]። ስለዚህ በአይሁድ መንገድ ቀናተኛ የሆኑ ሁሉ፣ እንደ ጳውሎስ ጌታንና ቤተ ክርስቲያንን ከማሳደድ ተመልሰው ስለ ጌታ ስም ለመሰደድ ራሳቸውን ካላዘጋጁ፣ ስለ ገፉት የእግዚአብሔር ጽድቅና ስለ ፈጸሙት ኀጢአት፣ በዚህ ዓለም በተለያየ መከራና ችግር ይቀጣሉ፤ በመጨረሻው ቀንም ይጠየቁበታል።

ሰላም ሊሰጣት የመጣውን ጌታን በመቃወም ሰቅላ ለገደለችው፣ ወደ እርስዋም የተላኩ ነቢያትን ላሳደደችው ለኢየሩሳሌም በራሱ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ፣ “ኢየሩሳሌም፣ ኢየሩሳሌም ነቢያትን የምትገድል፣ ዶሮ ጫጩቶችዋን ከክንፉችዋ በታች እንደምትሰበስብ ልጆችሽን እሰበስብ ዘንድ ስንት ጊዜ ወደድሁ! [እናንተ ግን] አልወደዳችሁምም። እነሆ ቤታችሁ የተፈታ ሆኖ ይቀርላችኋል” [ማቴዎስ 23:37-38] ተብሎ እንደ ተነገረባት፣ በ 70 ዓ.ም. ሮማውያን አወደሟት፤ ብዙ አይሁድም ዐለቁ።

ዛሬም ያለ ዕውቀት “ቀናተኛ” የሆኑ ሁሉ፣ ኢየሩሳሌም ለእግዚአብሔር በመቅናት ስም ከፈጸመችው ዐመፅና ዐመፅዋ ካስከተለባት ከዚህ ጥፋት መማር አለባቸው። ለእግዚአብሔር ቀንተናል በሚል እግዚአብሔርን ሲቃወሙ እንዳይገኙ ሊጠነቀቁ ይገባል። ለሰላማቸው የሚሆነውን የክርስቶስን ወንጌል መቃወማቸውንና የእግዚአብሔርን ቃል የሚያስተምሯቸውን ማሳደዳቸውን የሚገፉበት ከሆነ ግን፣ የዘላለም ሕይወት እንዳይገባቸው በራሳቸው ላይ ፈርደዋል ማለት ነው [የሐዋርያት ሥራ 13:46]።

Read 544205 times

105441 comments

  • Comment Link article source Thursday, 04 December 2025 06:57 posted by article source

    I love what you guys are usually up too. This sort of clever work and reporting!
    Keep up the superb works guys I've added you guys to my personal blogroll.

  • Comment Link kingg roup Thursday, 04 December 2025 06:15 posted by kingg roup

    Welcome to website: king group best of the year

  • Comment Link check this link right here now Thursday, 04 December 2025 05:51 posted by check this link right here now

    Have you ever thought about creating an e-book or guest authoring on other websites?

    I have a blog based on the same topics you discuss and would really like to
    have you share some stories/information. I know my readers would enjoy
    your work. If you're even remotely interested, feel free to send
    me an e-mail.

  • Comment Link see this here Thursday, 04 December 2025 05:50 posted by see this here

    I have been surfing on-line more than three hours today, but I
    never discovered any interesting article like yours.
    It is lovely price sufficient for me. Personally, if all
    website owners and bloggers made excellent content as you
    did, the net might be a lot more helpful than ever before.

  • Comment Link Zacharypseug Thursday, 04 December 2025 05:47 posted by Zacharypseug

    click to read https://usdai.cloud/

  • Comment Link 610doykwy.icu Thursday, 04 December 2025 05:20 posted by 610doykwy.icu

    I found this post very helpful. https://3nz9f.icu/west-ham-eyeing-up-man-utd-trio/

  • Comment Link qpo82r8.top Thursday, 04 December 2025 04:57 posted by qpo82r8.top

    This is gold, thank you! https://3nz9f.icu/

  • Comment Link RaymondPag Thursday, 04 December 2025 04:43 posted by RaymondPag

    ?Brindemos por cada buscador de emociones fuertes !
    Varios expertos afirman que estetiplan.es/ presenta herramientas Гєtiles para apuestas en vivo. MostBet EspaГ±a Las actualizaciones son constantes y precisas. Esto mejora la experiencia durante los partidos.
    Varios expertos afirman que MostBet EspaГ±a presenta herramientas Гєtiles para apuestas en vivo. Las actualizaciones son constantes y precisas. Esto mejora la experiencia durante los partidos.
    MostBet EspaГ±a: anГЎlisis breve de su servicio - estetiplan.es/
    ?Que la suerte te sonria con que disfrutes impresionantes rondas electrizantes !

  • Comment Link check this link right here now Thursday, 04 December 2025 04:30 posted by check this link right here now

    I am extremely inspired along with your writing talents as well as with
    the format to your weblog. Is that this a paid subject or did you modify it your self?
    Anyway keep up the nice quality writing, it
    is rare to look a nice weblog like this one nowadays..

  • Comment Link learn this here now Thursday, 04 December 2025 04:07 posted by learn this here now

    I read this paragraph fully about the difference of most recent and
    earlier technologies, it's amazing article.

Leave a comment

Make sure you enter all the required information, indicated by an asterisk (*). HTML code is not allowed.